Thursday, August 3, 2017

ሰበር መረጃ….. የብሄራዊ መረጃ እና የመከላከያ ወታደራዊ ደህንነቶች ከፍተኛ አሰሳ እያደረገ እንደሚገኝ ታምናኝ ምንጮች አሳወቁ – ልኡል አለሜ


  
By ሳተናውAugust 3, 2017 06:33



ሐምሌ 05/2009
Members of the Ethiopian army patrol
ክልል ስድስት እየተባለ በሚጠራዉ በቤንሻንጉል ጉምዝ በርታ አካባቢ ምስጥራዊ በሆነ ቅንጅት በመከላከያ ወታደራዊ ዘርፍ እና በብሄራዊ መረጃ የልዩ ስልጠና ክፍል ላለፉት 6 ወራት የአርበኞች ግንቦት 7 ወታደሮሮች ነን በሚል መልኩ ሲሰለጥኑ የነበሩ 9 ወጣቶችን ጭነዉ ወደ አሶሳ ሲጓዙ የነበሩ ሁለት ኮድ አ.አ ላንድ ክሩዘር ተሽከርካሪዎች የደረሱበት መጥፋታቸዉን ተንተርሶ የብሄራዊ መረጃ እና የመከላከያ ወታደራዊ ደህንነቶች በክልሉ ከፍተኛ አሰሳ እያደረገ እንደሚገኝ ታምናኝ ምንጮች አሳወቁ።
በተደጋጋሚ የአርበኞች ግንቦት 7ን ወታደሮች ማረኩኝ እንዲሁም እጅ ሰጡ  እያለ ፕሮፓጋንዳዉን የሚነዛዉ የህወሃት ቡድን እነዚህን 9 ሰልጣኞች ላለፉት 6 ወራት ኮነሬል ተስፋዬ በተባለ በኦሮምያ ክልል የአዲስ አበባን መስፋፋት ማስተር ፕላኑን በመቃወም በአምቦ ለተቃዉሞ ሰልፍ የወጡ ወጣቶችን በጭካኔ እንዲታደኑና ከፍተኛ ኢሰባዊ ግፍ እንዲፈጸምባቸዉ ትእዛዝ በመስጠት በሚታወቅ መኮንን ይሰለጥኑ የነበረ ሲሆን
በስልጠናዉ ላይ የመመሪያና የተዋረድ ንድፎችን በማዉጣት ኮነሬል ገብረ ዮሓንስ ግንባር ቀደም  የኦፕሬሽን ሐላፊ በመሆን በከፍተኛ ሚስጥር ይከዉኑት እንደነበር መረጃዎች ጠቁመዋል
ወጣቶቹ ለከፍተኛ የሽብር ተግባር የተቀናበሩና ከአዲስ አበባ እንዲሁም ከሰሜን ሸዋ የተመለመሉ ከፍተኛ የገንዘብ ወጪም የተደረገባቸዉ ነበሩ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

No comments:

Post a Comment