Monday, August 28, 2017

ታላቋ ትግራይን እንድለማመድ የተለቀቀው ካርታና የኢቢሲ ይቅርታ | ቬሮኒካ መላኩ


Filed under     



1~የEBC ን ውሃ የማያነሳ ማስተባበያና ይቅርታ አነበብኩት ። ፈረንጅ ሲተርት እንደዚህ ይላል “Fool me once, shame on you; Fool me twice, shame on me”…( አንድዬ ካታለልከኝ በአንተ አፍራለሁኝ ። ለሁለተኛ ጊዜ ካታለልከኝ ግን በራሴ ቂልነት አፍራለሁኝ ።) ይላል።

በእኔ በኩል EBC የሚያታልለው ንቃተ ህሊና ባለቤት ስላልሆንኩኝ “ይቅርታው ” ይለፈኝ።

2 ~ EBC የሚባለው ተቋም የራሱ የህውሃት እንደሆነ የታወቀ ነው። እንደ ራሱ ንብረት ሲጠቀምበት ነበር ። ፖሊሲውን ያስፋፋበታል። ማኒፌስቶውን ያራምድበታል። አማራን ይኮንንበታል።
በሌላ በኩል EBC ን ማመስገን ይገባል እንደዚህ ያለ ስሜት ኮርኩሮ የሚያቃጥል ድብቅ ሴራ እያቀረበ የደነዘዙ አማሮችን ቀስቅሶ ወደ አማራነት ካምፕ እንድቀላቀሉ ስለአነቃልን መመስገን አለበት።
ለማንኛውም ስህተቱ የተሰራው በፌስቡክ ሳይሆን በቴሌቪዥን ስርጭት ላይ በመሆኑ ይቅርታውም መጠየቅ ያለበት በቴሌቪዥን እንጅ ከጠቅላላው ህዝብ 1% የማይሞላ ህዝብ በሚጠቀምበት በፌስቡክ አይደለም።

3~ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተተክሎ አማራ ህዝብ ውስጥ የሚቀበር የ Time bomb ፋብሪካ ቶሎ ካልመከነ አማራ በአገሩ Homeless መሆኑ የማይቀር ነው ።
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የመምህርነትና የሰራተኝነት ጭምብል አጠልቆ አዲስ የፖለቲካ መልክአ ምድር ለመፍጠር ፕሮጄክት ቀርፆ አማራን ከባድና ሊወጣው የሚያስቸግር አደጋ ከመደቀኑ በፊት እንደት ማስቀረት እንደሚቻል ማሰብ አለብን።

4 ~የዚህ Time bomb ፋብሪካው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የቦምቡ ማፈንጃ እና መቆጣጠሪያ ሪሞት ኮንትሮል ደሞ የሚመረተው መቀሌ ነው።
አማራ አፍንጫህ ስር መሽጎ “የቦምቦች ሁሉ እናት ” እያመረተ የሚቀብርብህን “መርስኔሪ ” ቶሎ መፍትሄ ካልሰጠህው ማለቅህ ነው። እኛ አሁንም ተኝተናል እነሱ ግን 7ቱንም ቀናት እና 24 ሰአታት አማራን ለማጥፋት እየሰሩ ነው።

5~ አማራ ሆይ በየአመቱ ፣ በየወሩ ፣ በየሳምንቱ በየቀኑ ፣ በየሰአቱ ፣ በየደቂቃው እና በየሰከንዱ እየተሰረቀ እና እየተዘረፈ ያለውን ማንነታችንን ፣ መሬታችንና ርስታችንንርስታችንን ለማስመለስ በአንድ ላይ ካልቆምን መጥፋታችን ነው።

No comments:

Post a Comment