Saturday, July 22, 2017

ወያኔዎች የሰላሌ ዞን የፊቼ ከተማን የመብራት ሀይል ጣብያ ፈትተው ሲዘርፉ ነግቶባቸው ህዝቡ ደርሶባቸው

ባለፈው የአማራ ክልል መንግስት ወያኔ ስልጣን ከያዘ ምንም አዲስ የኤለክትሪክ ማስፋፊያ አልተሰራም ብሎ ሲያማርር ነበር። በኦሮሚያ ደግሞ ወያኔዎች የተተከለውን መንቀል ጀምረዋል::
#Ethiopiandj.com
ወያኔዎች የሰላሌ ዞን የፊቼ ከተማን የመብራት ሀይል ጣብያ ፈትተው ሲዘርፉ ነግቶባቸው ህዝቡ ደርሶባቸው አስጥሏል ይላል ከታች ያለው ዘገባ

በሰሜን ሸዋ ዞን በሰላሌ በፊቼ ከተማ...
የሚገኘውን የዞኑ እና የፊቼ መብራት ሀይል ጣቢያ በ12/11/2009 ምሽት ላይ የትግረኛ ቋንቋ ተናጋሪ የሆኑ ሰዎች ፈታተው በማወላለቅ በእንጨት አንድ ላይ አድርገው በማሰር በመኪና ለመጫን ዝግጅት ላይ እንዳሉ ስለነጋባቸው ህዝቡ በጩኽት ደርሶ አስጥሏል:: የተዘረፈውን የመብራት ሀይል እቃዎች ሊጭኑባቸው የነበሩት መኪናዎች የመንግስት ሲሆኑ የፌደራል ታርጋ የለጠፉ ሲሆኑ የተወሰኑት ሲያዙ ሌሎቹ አምልጠዋል::

በዚህ ዝርፊያ ላይ እያሉ በህዝቡ ርብርብ እጅ ከፈንጅ የተያዙት ሰዎች የትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ሲሆኑ ከሁለት ሰዎች በስተቀር ሌሎቹ ትግርኛ ቋንቋ እንጂ አይሰሙም:: በእጃቸው የያዙት ደብዳቤ ከፌደራል የተፃፈ እና የዚው ዞን አስተዳደር እና ከንቲባ ፊርማ ብቻ ያለው ነው:: እነዚህ ሰዎች ለግዜው ቁጥጥር ስር ቢውሉም የአጋዚ ጦር ሀይል ከፖሊስ እጅ ምሽት ላይ አስለቅቋቸዋል::
ከዚህ በፊትም በደርግ ዘመን ከተማዋን ሲያገለግል የነበረ ጀነሬተር በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጊዜ ወደ ትግራይ በውሰት ተብሎ ተወስዶ በዛው ደብዛው ጠፍቶ ቀርቷል::"
ምንጭ: ጅዋር Ethiopian DJ የኢትዮጵያ ሙዚቃ sitt bilde.Ethiopian DJ የኢትዮጵያ ሙዚቃ sitt bilde.ሙሃመድ

No comments:

Post a Comment