Thursday, July 20, 2017

አዲስ አበባ የሥራ ማቆም አድማውን ተቀላቀለች – ኮልፌ፣ አጠና ተራ፣ ሳሊተ ማሪያም ቤተክርስቲያን አካባቢ ሱቆች ተዘጋግተው ውለዋል


      




(ዘ-ሐበሻ) ከባለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ በተለያዩ ከተሞች እየተደረገ ያለው የሥራ ማቆም አድማ አዲስ አበባ ደረሰ:: ዛሬ በአዲስ አበባ በኮልፌ እፎይታ ፣ አጠና ተራና ሳሊተ ማርያም አካባቢ ሙሉ በሙሉ የንግድ ሱቆች ተዘግተው ውለዋል::
ሕወሓት የሚመራው መንግስት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የጫነውን አግባብ ያልሆነ ግብር በመቃወም ሕዝቡ በተለያዩ አካባቢዎች እንቅስቃሰዎችን እያደረገ ነው::

በአዲስ አበባ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር በሚደረግባቸው በኮልፌ ቀራኒዮ እፎይታ እና ታይዋን ገበያ ሕንጻዎች ሳይቀሩ ተዘግተው መዋላቸውን ከአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ዘግበዋል::
እንደምንጮቻችን ገለጻ  ሳሊተ ማርያም አካባቢም እንዲሁ ሱቆች ተዘጋግተው የሥራ ማቆም አድማ ተደርጓል::
በአዲስ አበባ ሳሊተ ማሪያም ቤተክርስቲያን  አካባቢ ያሉ ሱቆች በመዘጋት ላይ ናቸው:: አካባቢውን ፌደራል ፓሊስ ወሮታል:
የሕወሓት መንግስት ተላላኪዎች ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን እንዲከፍቱ የሚያስገድዱ መ ል እክቶችን ቢያስተላልፉም ነጋዴዎች እምቢታን መርጠዋል::

No comments:

Post a Comment