Wednesday, March 30, 2016

ወያኔዎች በሴይጣን ታስረዋል


| አባ ቢያ የባለሀገር ንቅናቄ
ለጋብቻ በማይመረጥበትና በማይታጭበት: ለቤት መስሪያ ዛፍ በማይቆረጥበት ጎዶሎ ወር ውስጥ የተወለደው ወያኔ: ዋጋው በቁና እየተሰፈረለት ነው:: ይህ የኃጥአት ልጅ ስብስብ ድርጅት የያዘው የዛር ፈረስ አምጥቶ እሞቱ ደጃፍ ላይ አድርሶታል:: ይኸው የሴይጣን መጫወቻ የሆነው ወያኔ በግድያ: በስርቆት: በዝርፊያ: በቅሚያ: በማጭበርበር: በማታለል: በመዋሸት አገርን ከነድንበሩ ትውልድን ከነባህሉ አበላሽቶአል:: ወያኔ ጫካ በነበረበት ጊዜ ሽፍቶቹን ለማነቃቃትና ለማዋጋት ሲል በሱዳን አማካሪነት Rhamnus Prinodes የተባለ ዕጸ-ፋሪስ ወይም የጌሾ ቅጠል በተለያየ ምግብና መጠጥ ውስጥ ጨምረው ወያኔ ሠራዊትን ያጠጡና ያበሉ ነበረ:: አመራሮች ሁሉ ጭምር ይጠቀሙ ነበረ:: በጎጃም የአብነት ተማሪዎች እንደዚሁም የአስኩዋላ ተማሪዎች ለትምህርት አእምሮን ያነቃቃል:: አንጎልን ይከፍታል እያሉ የሚወስዱትንና ከወሰዱ በሁዋላ በመጨረሻም አሳብዶ ከሰውነት ተራ የሚያወጣውን አብሾ ወይም በባዮሎጂ አጠራር ካናቢስ ሳቲቫ ወይም ማሪዋና በባህላዊ አጠራር ዕጸ-ፋሪስ ወይም አጤ-ፋሪስ ተብሎ የሚታወቀውን መርዘኛ ዕጸዋት ወያኔዎች ይጠቀሙ ስለነበር ዛሬ የወያኔ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ሁሉ አእምሮ ትክክል አይደለም:: ነገር ግን ማንም አልተረዳላቸውም እንጂ አእምሮአቸው ደንብሾአል ::ተቃውሶአል::
በዚህ የተነሳ ከጫካ የመጡ ነባሮቹ ወያኔዎች እርኩስ መንፈስ አጠናግሮአቸዋል:: ቁራና የተባለው ዲሞንስ ወይም መጥፎ መንፈስ የተጠናወታቸው ሰዎች ናቸው:: የሱዳን ቆሪጥ :ሌጌዎን: ጠጠር ጣይ: ዊቃቢ እና ከዘር ጭምር ወደልጅ የሚሸጋገረው Hobgoblins-Imps በአማርኛ አጠራር የዛር ውላጅ በወያኔዎች ላይ ሠልጥኖአል:: ዛሩ ባሪያዎቹ አድርጎአቸዋል:: እንደሚታወሰው ሁሉ ባለፈው ጊዜ የመንግሥት ቃለ-አቀባዩ የኦሮሞ ተቃዋሚዎችን ጋኔን የጠራቸው ብሎ ሲናገር ተደምጦአል:: ይህም ማለት ወያኔዎች በነዚህ እርኩስ መንፈስ ቁጥጥር ሥር ስለሆኑ ሁሉ ሰው እንደእነሱ ይመስላቸዋል:: የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ የሴይጣን መጫወቻ የሆነ ይመስላቸዋል:: እነሱ አንዴ የመጥፎ ማጂክ ባሪያ ስለሆኑ ::They are Slave Zar and they fear all bad magics. for example fools, Vagabond, mad poor,sick etc….ይህ ዓይነት አደጋ ያመጣብናል ብለው ስለሚጨነቁ በምድር ላይ ያለውን ወንጀል ሁሉ ይሠራሉ:: ጋኔን የጠራቸው ብሎ የተናገረው አፈ- ቀላጤው ጋኔን ጎታች The Demons puller የሆነው አለቃ መለስ ሁሉንም ወያኔ የገራው በዚህ መልክ ስለሆነ ነው:: ስለዚህ ወያኔዎች የሰው ህይወት የሚያጠፉት: የሰው ደም የሚያፈሱት: የሰው ልጅን የሚያሰቃዩት በጌቶቻቸው በእርኩስ መንፈስ እየታዘዙ: ለድፍረት ይሆናቸው ዘንድ አጤ ፋሪስ በጥብጠው እየጠጡ ስለሆነ ወደ ድርጊቱ የሚገቡት የሚያደርጉትን በሙሉ ለበጎ ያደረጉ ይመስላቸዋል:: ለዚህም ነው በሚዲያ ያለምንም ፍራቻ: ያለምንም ይሉኝታ ደረቅ ውሸት የሚዋሹት:: በዛር ፈረስ ላይ ስለሆኑ ሚሊዮን ሕዝብ አስር ሰዎች ብቻ መስለው ይታዩአቸዋል:: ሲገድሉ ደግ ያደረጉ ያህል ኮርተው ይናገራሉ:: ሲያሰቃዩ ያስታመሙ ይመስል ደረት ነፍተው ሕዝብ መኃል ይሄዳሉ:: ስለዚህም ነው ደህና ሰው ሳይታሰብ በድንገት ወያኔ ቤት አንድ ቀን ካደረ በዚያው ተበላሽቶ የሚቀረው:: ድምጻዊ ንዋይ ደበበ : ድምጻዊ ሰለሞን ተካልኝ እናም በርካታ አርቲስቶችና ጋዜጠኞች የወያኔ ባሪያ ሆነው የሚቀሩበት ዋናው ምክንያት በዚህ መሠረት ስለሚበላሹ ነው:: የተማሩ ስዎች ወያኔ ከሥራቸው ብታባሪራቸው እንኩዋን በየትም አገር ተቀጥረው መስራት የሚችሉ እንደነ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና ዓይነቶቹ የሱዳን ባህለዊ ጥበብ ሰለባ በመሆናቸው ነው:: እንደነ ልደቱ አያሌው ዓይነት የሴይጣን ተላላኪ ሆነው የቀሩት በዚህ መልክ ነው ::
ስለሆነም የኢትዮጵያ ሕዝብ ከነዚህ ሰዎች ጋራ ሰዎች ናቸው ብሎ ጤነኛ ንግግር ለማድረግ ሠላማዊ ድርድር መጀመር ዕርቅና ርትዕ ይኖራል ብሎ ማመን የሴይጣንን ችሎታና ባህርይ አለመረዳት ነው::
ማንኛውም ወያኔ አሙዋሙዋቱ ድንገት ነው:: ተቀጨ በሚባል ደረጃ ነው ሕይወታቸው የሚያልፈው:: ጄኔራል ኃየሎም ዐረአያ በመሸታ ቤት አንድ ተራ ሰው በዛገ መሣሪያ ተገደለ :: ሰላዩ ክንፈ ገብረ መድኅን በአንድ ረፋዱ ላይ ሰው ፊት ተደፋ:: ታምራት ላይኔ በመንግስት ምክር ቤት ፊት ቁጭ ብሎ እንደሕጻን ስመከር ስገጸጽ አልመለስ ብዬ ሰለነበረ እርምጃው ተገቢ ነው ብሎ መበላሸቱን ተናግሮ ከርቸሌ ተከረቸመ:: እሱ እንኩዋን የታሠረበትን የጋኔን ሰንሰለት በንስሀ ና በጸሎት በጥሶ ዛሬ ሰው ሆኖአል:: የአቶ መለስ እና የአባ ጳውሎስ ጉዋደኝነትና የሠፈር ልጅነት በዚያ ላይ ቅዱስ አባት በሚያስብል ከፍተኛ ማዕረግ ላይ ሆነው ሲሠሩ የነበረው ክፉ ሤራና ሥራ የአቶ መለስ ጠቅላይ አዛዥነት ሚና ተደምሮ ኢትዮጵያ በእነዚህ በሁለቱ አደዋኛዎች ጫማ ሥር እንደወደቀች ሲታሰብ ሴይጣን በተቀደሰችው ኢትዮጵያ ላይ ምን ዓይነት ሹመት እንደነበረው መረዳት አያስቸግርም:: ነገር ከሴይጣንና ከጋኔን ጋራ ጨዋታው የሚባለው:: ከመቃብር
መጨረሻ አያምርም እና ሁሉቱም ሞቱ ሳይሆን ተቀሰፉ ነው የሚገርም ነገር ደግሞ አንዱ አንዱን እንዳይቀብር ሆነው ነው የወረዱት ::
የሴይጣን ሥራ ይኸው ነው:: ሴይጣን ውለታ አያውቅም:: ሰይጣን ቤት ምህረት የለም :: ሰብዓዊ ስሜት ጋኔን ቤት ከተገኘ ሰብዓዊ ስሜት የተሰማው ሰው ወዲያው ይቀሰፋል:: እነዚህ የቀሩቱ ጋኔን የሚጋልባቸው ወያኔዎች ከሰውነት ውጭ ናቸው:: ሲቀኑ: ሲጨክኑ: ሲዋሹ :ሲያታልሉ: ሲገድሉ :ሲያሰቃዩ: ሲጠጡ: ሲሰከሩ: ሲያመነዝሩ በጤናቸው አይደለም:: እላያቸው ላይ ያረፈው የጋኔን አለቃ እየተጫወተባቸው ነው:: በየቀኑ ጠርሙስ ሙሉ ዕስኪ መጨረሰ: በየቀኑ ከተለያየ ሴት ጋራ መተኛት ና እርካታ ማጣት የበረሃ አጋንንት ባህርይ ነው:: በዚህ ላይ የወያኔዎችን ፊት ተመልከቱ እስቲ:: እህልና ውሃ ከቀመሱ ወራት ያለፋቸው ወይም ለኮሶ ሽረት እንቆቆ የሚጠጡ የሚመስል ፊት ነው የሚታየው:: የጤናማ ሰው ፊት እኮ አይደለም ፊታቸው:: የበረከትንና የሰብሀት ነጋን ፊት ተመልከቱ:: በደርግ ዘመን በሕብረት ዘመቻ የተሠራ እርከን ነው የሚመስለው:: አርከቤን ተመልከቱት:: ኦፋይት ዑቃቢ ያለበት ይመስላል:: ሁሎቹም ወያኔዎች በየቀኑ ገርጥጠው እና ገርኝተው ይታያሉ :: የሰው ልጅ ሀመልማል ፊት የላቸውም ::
እናም ኢትዮጵያ በሴይጣን በአጋንንት አገዛዝ ሥር ስለሆነች ከተቻለ በእግዚ- ኦታ በጸሎት ካልሆነም በአንድነት ተነስቶ ይህንን ደም መጣጭ የሴጣን ጋማዎችን ማስወገድ ይኖርብናል :: እንደሰው እያዩ ለምን ህግን ጣሱ? ለምን እግዚአብሄርን አልፈሩም? ለምን ባህላችንን ተጻረሩ? ብሎ መታለል ይብቃ:: ምንም ዓይነት ከስይጣና ባሪያዎች ጋራ ንግግርና ድርድር አለማድረግ ትልቅ ውሳኔ ነው ::

No comments:

Post a Comment