Monday, May 2, 2016

ገብረመድህን ኃይሌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ ሆነ



Geberemedhin(ዘ-ሐበሻ) ባለፈው ሳምንት ዘ-ሐበሻ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌን ኢትዮጵያ ከእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት ማባረሯን ከዘገበች በኋላ ዛሬ ፌዴሬሽኑ በይፋ አሰልጣኙን ማባራሩን ገልጿል:: የብዙዎች ጥያቄ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ማን ይረከብ ይሆን? የሚለው ነበር:: እንደ ዘ-ሐበሻ ምንጮች ዘገባ ከሆነ የቀድሞው የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋች አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ጊዜያዊ አሰልጣኝ ሆኖ ተመርጧል::
በ1977 ዓ.ም የብሔራዊ ቡድናችን አምበል የነበረው አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ የመከላከያ ስፖርት ክለብን ከ2004 ጀምሮ ሲያሰለጥን ቆይቷል:: ገብረመድህን ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ 2 ጨዋታዎች የቀሩትን ብሔራዊ ቡድናችንን ይዞ እነዚህን ጨዋታዎች እንደሚያደርግም ይጠበቃል::


ገብረመድህን ኃይሌ የቅዱስ ጊዮርጊስ ኮከብ ተጫዋችም ነበር::

No comments:

Post a Comment