(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይለማርያም ደሳለኝ ለህክምና ጀርመን መግባታቸው ተሰማ:: በጀርመን ግራንድ ደቺ ባደን ከተማ ውስጥ መኖሪያ ቤት ገዝተው እንዳስቀመጡ የሚነገርላቸው ኃይለማርያም ከኢትዮጵያ የወጡት ለ እረፍትና ለህክምና በሚል በግል አውሮፕላን በመከራየት ነው::
ጠቅላይ ሚኒስተሩ በጀርመን ቆይታቸው ዓይናቸው አካባቢ ቀዶ ጥገና (Aesthetic surgery) በማድረግ ፊታቸውን በፕላስቲክ ሰርጀሪ ያስተካክላሉ ተብሏል:: እንደ ዜና ምንጮች ገለጻ በታዋቂ የዓይን እና የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ሃኪሞች ክሊኒክ ውስጥ ዓይናቸውን እና ፊታቸውን ውበት እንደሚያሰሩ ገልጸዋል::
ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርባት ባደን ከተማ ሃብታሞች የሚኖሩባት ከተማ ስትሆን ቤትና ንብረት በዚህ ከተማ ለማፍራት በጣም ሃብታም መሆን ቢያስፈልግም ሃይለማርያም ግን በዚህ ከተማ ውስጥ የቤት ባለቤት ናቸው::
No comments:
Post a Comment