Friday, April 8, 2016

በድርቁ ምክንያት ከሰቆጣ ወደ ደብረብርሃን የሰፈሩ ወገኖች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተነገራቸው


Zehabesha News
በድርቁ ምክንያት ከሰቆጣ ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን ውስጥ የሰፈሩ ከ250 አስከ 300 የሚሆኑ ዜጎች በዛሬው እለት በደብረ ብርሃኑ መስተዳድር ወደመጡበት እንደሚመለሱ ማሳሰቢያ እንደተሰጣቸው ታወቀ::
ስደተኞቹ ወደ መጡበት ከተመለሱ ለእነሱም ሆነ ለልጆቻቸው የሚጠብቃቸው ሞት እንደሆነ በመግለፅ ለወገን የድረሱልን ጥሪ አስተላልፈዋል።
የደብረ ብርሃን ህዝብ ስደተኞቹን በአቅሙ ለመርዳት የበኩሉን ጥረት እያደረገ ሲሆን ሕወሓት የሚመራው መንግስት ቀጭን ትዕዛዝ በስደተኞቹ ላይ በተላለፈው ኢ-ሰብአዊ ውሳኔ ክፉኛ ልቡ መሰበሩን ከአካባቢው ከስፍራው እየመጡ ያሉ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የመላው አማራ ህዝብ ለእነዚህ ሞት ለተፈረደባቸው ወገኖቹ ድምፅ በመሆን በነፍስ እንዲደርስላቸው የአማራ ሕዝብ አክቲቭስቶች እንቅስቃሴ ጀምረዋል::

No comments:

Post a Comment