Saturday, April 9, 2016

የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር ዜናዎ

 

ርዕሰ ዜና
·         የእስራኤል መንግስት ተጨማሪ ቤተእስራኤሎች ወደ እስራኤል እንዲገቡ ፈቀደ
·         በጂቡቲ ምርጫ እየተካሄደ ነው
·         በሊቢያ የአሲስ አባላት ቁጥር እየጨመረ መጣ ተባለ
·         የሴየራ ሊዮን ፕሬዚዳንት የውጭ ባለሀብቶችን ተማጸኑ
·         ሞሮኮ የውጭ ዜጎች ከሀገሯ አባረረች
መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም.
Ø ተጨማሪ የቤት እስራዔሎች ቤተሰቦች በዚህ አመት ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ሊመጡ ስለሚችሉበት ሁኔታ የእስራዔል ገዥ ፓርቲ ከአጋሮቹ ጋር ስምምነት የደረሰ መሆኑን ሐሙስ መጋቢት 29 ቀን ማምሻውን በሰጠው መግለጫ ገልጿል። በዚህ 1300 የሚሆኑት እንዲመጡ የተፈቀደ ሲሆን ወደፊት ቁጥሩ  ከዚህ በላይ ሊጨምር የሚችል መሆኑን ተገልጿል። ባለፈው ወር በእስራዔል አገር የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዘመዶቻቸው ወደ እስራኤል እንዲመጡ በመጠየቅ ከፍተኛ ትዕየንተ ሕዝብ ማካሄዳቸው የሚታወስ ሲሆን የእስራዔል መንግስት ነገሩን ችላ በማለት ኢትዮጵያውያኑን  የፈቃዱን ውሳኔ ሲያስተላልፍ መቆየቱ ይታወሳል። ባለፉት ጥቂት ቀናት አንዳንድ የፓርላማ አባላት ባደረጉ ጥረትና እንዲሁም ተቃውሞውና አድማው የጋራ መንግስቱን ህልውና አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል መሆኑ ስለገባው  ገዥው ፓርቲ ሀሳቡን ቀይሮ ቤተእስራኤሎቹ ወደ እእስራኤል እንዲመጡ ፈቅዷል።
File Photo
File Photo
 
Ø በጂቡቲ ዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2008 ዓም  ጠቅላላ ምርጫ እየተካሄደ ሲሆን የጂቡቲው ፕሬዚዳንት አሸናፊ ሆነው እንድሚቀርቡ አስቀድሞ ታውቋል። ስድስት ተወዳዳሪዎች ለምርጫው ቢቀርቡም ላለፉት 17 ዓመታት በስልጣን ላይ የቆዩት ፕሬዚዳንት አሸናፊ እንደሚሆኑ ጥርጥር የለውም በማለት ታዛቢዎች ይተቻሉ። ከተቃዋሚዎች ውስጥ የተወሰኑት በምርጫው ላለመሳተፍ የወሰኑ ሲሆን ተወዳዳሪ ሆነው የቀረቡት ደግሞ የፖሊሶች አፈና መጠናከሩንና የመገናኚያ ብዙሃን አድላዊነትን በመግለጽ ክስ እያሰሙ ይገኛሉ። ድምጹን የሚሰጠው  የጂቡቲ ሕዝብ ቁጥር አነስተኛ ነው የተባለ ሲሆን ፕሬዚዳንት ጉሌህ ከየመን የመጡ ስደተኞችን አስመዝገበው ድምጽ እንዲሰጡ እያደረጉ ነው ተብሏል። የተቃዋሚዎች መከፋፈል ጉሌህን ሊጠቅም ችሏል የሚሉ አልጠፉም። ከሶስት አመት በፊት የጉሌህ ተቃዋሚ የሆኑ ፓርቲዎች ትብብር ቢፈጥሩም ጉሌህ ተወዳድሮ ሊያሸንፍ የሚችል አንድ የጋራ ተወዳዳሪ ማውጣት ላይ ሊስማሙ አልቻሉም።  የምዕራብ አገሮች ጂቡቲ ውስጥ ባላቸው ጥቅም ምክንያት ስለምርጫው አስተያየት ሲሰጡ አይሰማም።
 
 
Ø በሊቢያ የአይሲስ አባላት ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን በአፍሪካ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋም አዛዥ ተናገሩ። አዛዡ ላለፉት 12 እስከ 18 ወራት ባሉት ጊዚያት ወደሊቢያ የገቡት የአይሲስ አባላት ቁጥር ከ4 ሺ ወደ 6 ሺ ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸው አሸባሪዎቹ በብዛት ሊገቡ የቻሉት በአገሪቷ ውስጥ ያለውን የፖለቲካ እና የጸጥታ አለመረጋጋት ተጠቅመው ነው ብለዋል። አብዛኞቹ ከውጭ የመጡ በመሆናቸውና አገር በቀል የሆኑ አባሎች አነሰተኛ በመሆናቸው እንደ ኢራክና እንደ ሶሪያ የተወሰነ ክልል ይዘው ለመቆጣጠር አይችሉም የሚል አስተያያት አዛዡ ጨምረው ገልጸዋል። በሊቢያ የሚገኙት ልዩ ልዩ የሚሊሺያ ቡድኖች በየቦታው ከአይሲስ ኃይሎች ጋር እየተጋጩ ስለሆነ በራሳቸው የሚጠናከሩበት ሁኔታ አነስተኛ መሆኑን ይናገራሉ።
 
Ø የሴየራ ሊዮን ፕሬዚዳንት በአገራቸው የኢቦላ በሽታ የታደከመ መሆኑን ገልጸው የአገሪቷ ኢኮኖሚ ከወደቀበት ቦታ እንዲያንሰራራ ለማደረግ የውጭ አገር መዋእለ ንዋይ እንደሚያስፈልግ ተናገሩ። ከምዕራብ አፍሪካ አገሮች 11 ሺ ዜጎችን የገደለው የኢቦላ በሽታ የሲየራ ሊዮንን ኢኮኖሚ በተለይም የእርሻውን መስክ ክፉኛ ያጠቃው በመሆኑ የውጭ አገር ሀብታሞች ገንዘባቸውን በልዩ ልዩ የስራ መስክ ላይ በማዋል ኢኮኖሚው እንዲያንሰራራ እንዲያደርጉ ተማጽነዋል። ፕሬዚዳንቱ በቅርቡ ቱርክ ውስጥ  በሚደረገው የእስላማውያን አገሮች አመታዊ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ተመሳሳይ ልመና የሚያቀርቡ መሆናችውን ገልጸዋል። 
 
Ø የሞሮኮ መንግስት 8 የውጭ አገር ዜጎችን ከአገሩ ያባረረ መሆኑን ገለጸ። ተባረሩ የተባሉት ግለሰቦች ሁለት የፈረንሳይ አንድ የቤልጂክ እና አምስት የስፔይን ዜጎች ሲሆኑ ለመባረራቸው ምክንያት የሆነው በእስር ላይ ለሚገኙት የምዕራብ ሳህራ ዜጎች እርዳታና ትብብር አድርገዋል የሚል ነው። ከስድስት ዓመት በፊት ግድም ኢዚክ (Gdem Izik) በሚባለው በምዕራብ ሳህራ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ የተቀጣጠለው ዓመጽ  ከሞሮኮ የጸጥታ ኃይሎች ጋር በተፈጠረ ግጭት 11 ፖሊሶችና ሁለት ሰላማዊ ሰዎች መገደላችው አይዘነጋም። ፖሊስ  አመጹን ለማስቆም  ካምፑ እንዲፈርስ ያደረገ ሲሆን በርካታ ሰዎችን ወስዶ ማስሩ ይታወቃል። ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለው ድርጅት ባለፈው ህዳር ወር ተይዘው የሚገኙት የምዕራብ ሳህራ ዜጎች እንዲፈቱ መጠየቁ ይታወሳል።
 
 
Ø በዳርፉር አካባቢ የሽብር ተግባር ፈጽመዋል በሚል ክስ አንድ የሱዳን ፍርድ ቤት በ22 የደቡብ ሱዳን ዜጎች ላይ የሞት እና የእድሜ ልክ እስራት ቅጣት የበየነ መሆኑ ተገልጿል። ክስ የቀረበባቸው 22 ሰዎች ጀስቲስ ኤንድ ኢኩዋሊቲ ሙቭመንት የሚባለው የዳርፉ አማጽያን ቡድን አባላት ሲሆኑ ድርጅቱ ከሶስት አመት በፊት ከሱዳን መንግስት ጋር የእርቅ ስምምነት ፈርሞ የተቃውሞ እንቅስቃሴውን ማቆሙ ይታወቃል። ባለፈው ጥር ወር 22 የደቡብ ሱዳን ዜጎች የአማጽያኑ ድርጅት አባል ሆነው መንቀሳቀሳቸው በመጋለጡ የውጭ አገር ዜጎች በመሆናችው ብቻ በቁጥጥር ስር ውለው ለፍርድ እንዲቀርቡ ተደርጓል። ባሁኑ ጊዜ በደቡብ ሱዳን እና በሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ከምንጊዜውም በላይ ዝቅተኛ ሆኖ የሚታይበት ሲሆን በሰዎቹ ላይ የተበየነው የፍርድ ውሳኔ የሁለቱን አገሮች ግንኙነት ይበልጥ ሊያሻክረው እንደሚችል ተገምቷል። የአለም አቀፉ ፍርድ ቤት በፕሬዚዳንት በሽር ላይ የወንጀለኛነት ክስ ለመመስረት ምክንያት በሆነው በዳርፉር ጦርነት 300 ሺ ሰው ያህል ህይወቱ ሲጠፋ ከ2.5 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከቤት ንብረቱ ተፈናቅሎ ስደተኛ መሆኑ ይታወቃል።
 

No comments:

Post a Comment