Tuesday, April 12, 2016

ዲና በአዲሱ ክሊፗ እጆቿን ወደ ላይ በማጣመር በኦሮሚያ ለተነሳው ሕዝባዊ ቁጣ አጋርነቷን አሳይታለች ማለት ይቻላል




dina anteneh
dina bede
ስንታየሁ ከሚኒሶታ
“አልችልም” የሚል ነጠላ ዜማ ነበር በቅድሚያ የለቀቀችው:: በዚህ ዘፈን እንደተዋወቀች “ጋሜ” የተሰኘ በስታይል የተሰራ ዘፈኗን አስከትላ ስታበቃ “ናማ” በሚለው ዘፈኗ ሰቀለች – ዲና አንተነህ:: ሰሞኑን ደግሞ ‘በዴ’ የተሰኘና በአማርኛ እና በኦሮሚኛ ቋንቋ የተሰራውን ዘፈኗን ለቀቀችልን:: ይህ ዘፈን ዘ-ሐበሻን ጨምሮ በተለያዩ ድረገጾች ላይ የተለቀቀ ሲሆን እነዚህን ሳይጨምር በአንድ የዩቲዩብ ቻናል ላይ በሁለት ቀናት ብቻ ከ78 ሺህ በላይ ተመልካቾችን በማግኘት ሪከርዱን ይዟል::
እንደ እኔ አስተያየት ዲና በዚሁ አዲሱ ነጠላ ዜማዋ እጇቿን ወደላይ በማጣመር ከኦሮሞ ተማሪዎች ሰሞኑን ካነሱት ሕዝባዊ ቁጣ ጋር ያላትን አጋርነት አሳይታለች ማለት ይቻላል:: :: በተለይም በክሊፑ ላይ እጆቿን ወደ ላይ ያጣመረችበት ቦታ ላይ ከጀርባ ያለው ቦታ የመቃብር ቦታዎች ይመስላሉ:: ይህም በኦሮሚያ ክልል በሕወሓት መንግስት ለተገደሉት ንጹሃን መታሰቢያ ለማድረግ የታሰበ ያስመስለዋል:: እንዲህ ነው ጥበብ መል ዕክት ማስተላለፊያ ሲሆን::
ይህን የዲናን ሁኔታ አይተው መንግስታዊ ሚዲያዎች እንደለመዱት ዘፈኑን በሚድያዎቻቸው እንደማያስተላለፉት ይጠበቃል:: በድጋሚ ዘፈኑን ተመልከቱት::

No comments:

Post a Comment