Tuesday, June 27, 2017

ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም የኢትዮጵያ ምድር ላይ ልዩ ጥቅም አለው! የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ የሕወሓት ሀገር ከፋፋይ ቀጣይ አጀንዳ አካል ነው


       




ጉዳያችን / Gudayacnhn
ሰኔ 21/2009 ዓም (ጁን 28፣2017)
++++++++++++++++++++
ዛሬ ሰኔ 20፣2009 ዓም የሕወሓት ሚኒስትሮች ምክር ቤት የኦሮምያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ የሚኖራት ጥቅም በሚል ርዕስ ውሳኔ ማሳለፉ እና የሕወሓት ኢህአዴግ  99% አሸነፍኩ ወዳለበት ምክር ቤት እንደሚመራ ተነግሯል። ጉዳዩ ልዩ መብት የሰጠ የመሰለው ካለ እርሱ ከ26 አመታት በኃላም ገና ፖለቲካ ሀ ሁ እያለ እንደሆነ መረዳት ያለበት ይመስለኛል።
file photo
1/ ልዩ ጥቅም የሁሉም ኢትዮጵያዊ መብት አይደለም እንዴ?
 
ልዩ ጥቅም የሚለው አባባል በእራሱ የመከፋፈል አላማ ያነገበ አባባል ነው።አንድ ሰው ልዩ ጥቅም ለማግኘት ዋናው መሰረት ሊሆን የሚገባው በኢትዮጵያዊነቱ ነው እንጂ የታሪክ የበላይነት ወይንም የዘር መሰረቱ ወይንም የተለየ አነጋገር በመናገሩን መሰረት አድርጎ የሚሰጥ ከሆነ መከፋፈል ነው።ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም የኢትዮጵያ ምድር ላይ ልዩ ጥቅም ሊኖረው ይገባል። ልዩ የሚያደርገው ደግሞ ከኢትዮጵያ ምድር በመውጣቱ ነው።ከጃፓን ወይንም ብራዚል የመጣ ሰው የማይኖረው ልዩ ጥቅም ኢትዮጵያዊ ሊኖረው ይገባል።ይህ ማለት ኦሮሞው አዲስ አበባ ላይ በኢትዮጵያዊነቱ ልዩ ጥቅም እንደሚኖረው ሁሉ አዲስ አበቤውም በኦሮምያ ላይ ልዩ ጥቅም አለው።ኦሮሞው በመቀሌ ላይ ልዩ ጥቅም እንደሚኖረው ሁሉ የአክሱሙም ሰው በኦሮምያ ላይ ልዩ ጥቅም አለው።የወለጋው ገበሬ በጎንደር ላይ ልዩ ጥቅም እንዳለው የራስ ዳሽን ገበሬም በነቀምት ላይ ልዩ ጥቅም አለው።ይህ ሁሉ ልዩ ጥቅም የሚመነጨው እንደ ህወሓት የሚኒስትሮች ምክር ቤት በከፋፋይ አጀንዳ ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በኢትዮጵያዊነት ሙሉ መብት ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጋ እና መሬት በሁሉም የኢትዮጵያ መሬት ላይ ልዩ ጥቅም አለው።የኦሮምያ ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ የሚለው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ  በእራሱ ከፋፋይ የሆነው  የስርዓቱ አጀንዳ ቀጣይ ምዕራፍ ነው።
2/ የውሃ ፍሳሽ አገልግሎት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚሰጥ አገልግሎት አይደለም እንዴ?
 “የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት በአዲስ አበባ ዙርያ ላሉ የኦሮምያ ክልሎች ያካተተ ይሆናል” ይላል ከአዋጁ አካል ውስጥ አንዱ።አሁንም ውሃ የማግኘት ልዩ መብት የሁሉም ኢትዮጵያዊ መብት ነው።ይህ አዋጅ ባይወጣ ኖሮ በኢትዮጵያዊነቱ በአዲስ አበባ ዙርያ ያሉ የኦሮምያ ክልሎች የውኃ አገልግሎት ላያገኙ ነበር? የውኃ ፍሳሽ አገልግሎት ለማግኘት የልዩ ጥቅም አዋጅ ባይወጣ ኖሮ በኢትዮጵያውነታቸው የማግኘት መብት የላቸውም ነበር? ይህ በእራሱ ከፋፋይ አቀራረብ ነው።በአዲስ አበባ ዙርያ ያለ የኦሮሞ ሕዝብ ውሃ ለማግኘት ልዩ አዋጅ መጠበቅ ነው ያለበት ወይንስ በኢትዮጵያዊነቱ የሚያገኘው መብት ነው መሆን ያለበት? ለአዲስ አበባ ውሃ ፍሳሽ አገልግሎት ወጪ የሚሸፈነው  ቀረጥ  ከኦሮምያ የሚመጣ ገንዘብም ጭምር መሆኑን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሊያረሳሳን ነው ? እናስ የአዲስ አበባ ዙርያ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ገና ለገና ከአዲስ አበባ ሕዝብ ጋር አብሮ ይነሳብኛል ልከፋፍለው በሚል እሳቤ ውሃ በልዩ ጥቅም አዋጅ መሰረት ይዘረጋልሃል የሚል አዋጅ ረቂቅ አንድ ሐሙስ የቀረው እና የታመመ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ካልሆነ ማን ያወጣዋል?
3/ የጤና አገልግሎትስ የሁሉም ኢትዮጵያዊ መብት አይደለም እንዴ?
 
በአዋጁ ረቂቅ ላይ “አዲስ አበባ ወይም ፊንፊኔ የኦሮሚያ ክልል ዋና ከተማ በመሆኗ በከተማዋ የሚሰጠው የጤና አገልግሎት በከተማዋ ዙሪያ ያሉ የክልሉ ተወላጆችን ታሳቢ ያደረገ ይሆናል” ይላል። የጤና አገልግሎት የኢትዮጵያዊነት ልዩ ጥቅም ነው።ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍልል ቢኖር የጤና አገልግሎት የማግኘት መብቱ ነው።በእዚህ ረቂቅ ላይ አዲስ አበባ እና ኦሮምያ የተለያዩ ሀገሮች ይመስል በአዲስ አበባ የሚሰጠው የጤና አገልግሎት በከተማዋ ዙርያ ያሉ የክልሉ ተወላጆች ታሳቢ ያደርጋል ሲል ዛሬ ተነስቶ ልዩ ጥቅም የሰጠ አስመስሎ ሕዝብ የመከፋፈል አላማ ለማሳካት ብቻ የተገለፀ ነው።
4/ የአዲስ አበባ ሕዝብ እና የኦሮምያን ሕዝብ ከህወሓት በበለጠ ይተዋወቃል 
በእዚህ ረቂቅ አዋጅ ላይ የአዲስ አበባ ስም በፊንፊኔ፣የከተማዋ አንዳንድ ቦታዎች እና አደባባዮች በኦሮምያ ታሪክ ይቀየራሉ የሚል ሃሳብ የያዙ አረፍተ ነገሮች እንዲሁም ኦሮምኛ ከአማርኛ ጋር የስራ መጠቀምያ ይሆናል ይላል።ኦሮምኛ የስራ መጠቀምያ መሆኑ አማርኛ እስካልገባው ድረስ ኦሮምያ የተወለደ ኢትዮጵያዊ በኦሮምኛ አገልግሎት ማግኘቱ ሙሉ መብቱ ነው።ዛሬ ህወሓት እንደ ልዩ ጥቅም አድርጎ ማቅረቡ ነው የማይመቸው። ይህ እንዴት ልዩ ሆኖ ይቀርባል? ኢትዮጵያዊ መብቱ በሚለው ስር የሚገባ ነው።አንድ የጋምቤላ ተወላጅ አዲስ አበባ መጥቶ አማርኛ ካልገባው በጋምቤላ አነጋገር አገልግሎት የማግኘት መብቱ ኢትዮጵያዊነቱ ያጎናፀፈው መብት ነው እንጂ ልዩ መብት ሊባል ያችልም። ሕወሓት ለመከፋፈል ስትፈልግ ልዩ መብት ብላ ትርክት መጀመሯ አስቂኝ ነው። የአዲስ አበባ ስያሜ መቀየር እና የከተማዋን ታሪካዊ ቦታ ከመቀየር አንፃር የተነሳው አገላለጥ በእራሱ የተደናበሩ ሰዎች ያወጡት ረቂቅ አዋጅ ነው። በመጀመርያ ደረጃ በአዲስ አበባ ውስጥ የተሰጡት ስሞችም ሆኑ የአዲስ አበባ የእራሷ ስያሜ እውን ታሪካዊ አመጣጥ የሌለው ባዶ ትርክት ከነበረ የታሪክ ሰዎች ይንገሩን እና እንመን።በሐሰት ታሪክ ግን የትም ሀገር ስም አይቀየርም። ይህንን ልሞክር የሚል ካለ የመስቀል አደባባይ እና የአብዮት አደባባይ ስያሜን ማስታወስ ነው።በሕልም እና በስሜት ሕዝብ ያጋጭልኛል ከሚል እሳቤ ብቻ ሕወሓት ይህንን ማሰቧን እራሱ የኦሮሞ ሕዝብ እና የአዲስ አበባ ነዋሪ ጠንቅቆ ይረዳል።
ባጠቃላይ ልዩ ጥቅም በሚል ቡልኮ የተሸፈነው የህወሓት ሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ አዋጅ አዲስ አበባ እና ኦሮምያን የተለያዩ ሀገር በማስመስል የአዲስ አበባ እና ዙርያዋን ያሉት የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ግንኙነት ኢትዮጵያዊ የሆነ የጋራ እሴት ሳይሆን የጥቅም ግንኙነት ብቻ ያላቸው  አስመስሎ የማቅረብ ሙከራ ነው።መንግስት የተባለ አካል የመጀመርያ ስራው ዜጎቹን በእኩልነት የማስተዳደር፣ሕግ የማውጣት እና የማስፈፀም አቅሙን የማስመስከር  መሆን ይገባው ነበር።ከእዚህ ውጭ አንዱን አስነስቶ በእዚህ አካባቢ ልዩ ጥቅም አለህ።አንተኛው ግን በምትኖርበት ከተማ ከእርሱ ያነሰ ጥቅም ነው የምታገኘው የሚሉ አባባሎች በእራሳቸው ህዝብን ለመከፋፈል የሚደረጉ አጀንዳዎች የማስቀጠል ሥራ አካል ካልሆኑ ሌላ ሊሆኑ አይችሉም። አዲስ አበባ እና ኦሮምኛ ተናጋሪውን ኢትዮጵያዊ ለመከፋፈል አትሞክሩ።ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም የኢትዮጵያ ምድር ላይ ልዩ ጥቅም ሊኖረው ይገባል። ሕዝብ የምታገለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በኢትዮጵያዊነቱ እኩል ልዩ ጥቅም እንዲኖረው ነው።
ይህንን ፅሁፍ የምደመድመው አንድ የኦሮሞ ማኅበረሰብ አክቲቪስት በተናገረው ንግግር ነው። አባበሉ አሁን ሕወሓት እየዳከረበት ካለው የመከፋፈል ከንቱ ሥራ ፍሬ እንደሌለው በሚገባ ያሳየ ነው። አክትቪስቱ ያለው እንዲህ ነበር
“ሕወሓት የኦሮሞ ማሕበረሰብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር ያለውን ማኅበራዊ፣ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ትስስር በመቶዎች በሚቆጠሩ  ዓመታት ውስጥ ያለፈ እና ጠንካራ የደም ትስስር መሆኑን ህወሓት በደንብ ያወቀው አይመስለኝም።እነርሱ ራቅ ካለ አካባቢ ስለመጡ የእዚህ አይነቱ ጠንካራ ግንኙነት ታሪክ በደንብ የገባቸው አልመሰለኝም።የኦሮሞ ሕብረተስብ አሁን ሕወሓት እለያይበታለሁ እያለ የሚያቀርባቸው አጀንዳዎችን የመለያያ አጀንዳዎች እንደማይሆኑ ጥንት በሰራቸው ስርዓቶች ካፈረሳቸው ቆይቷል።ሕወሓት ትልቅ የመረጃ ክፍተት ላይ እንዳለ መረዳት አለብን” ነበር ያለው።

Friday, June 23, 2017

የ34 ኢትዮጵያውያን ጉዳይ በኬንያ – ጥላየ ታረቀኝ


By ሳተናውJune 23, 2017 03:17



የ34 ኢትዮጵያውያን ጉዳይ በኬንያ – በሀገራችን ኢትዮጵያ ህገ-ወጥ የሰዋች ዝውውር ከፍተኛ የሆነ ጉዳት እያመጣና እያደረሰ መሆኑን ንፁሀንንና በእድሜ ያልጠነከሩ ለጋ ወጣቶችን እያረገፈ መሆኑን ለኢትዮጵያንና በዚህ ማህበራዊ ድህረ ገፅ ላይ ላላችሁ ወገኖቼ መንገር ለቀባሪ ማርዳት ይሆንብኛል ለምሳሌ በሊቢያ በግብፅ ሲና በርሃ በሜዲትራኒያ ባህር እንደጉድ የሚረግፉ ወገኖቻችን ቁጥር ቤት ይቁጠረው ይሄ ህገወጥ የሰዋች ዝውውር ጉዳዩ ያላንኳኳው ቤት የለምና ሁሉንም አንገት ያስደፋ ጉዳይ ነው።
ከኢትዮጵያ ደቡብ ክልል በዚህ ባሳለፍነው ሳምንት 34 ኢትዮጵያውያን በሞያሌ በኩል በማድረግ በህገወጥ የሰዋች አዝዋዋሪ ወይም ሰው በቁሙ በሚሸጡ የሰው ነጋዴዋች አማካኝነን ኬንያ ይገባሉነገሩን ከመነሻው ከሀገራቸው ኬንያ መግቢያ ቦርደር ጀምሮ ሲከታተል የነበረው የኬንያ ፓሊስ እነዚህን ወጣቶች ከናይሮቢ ወጣ ብሎ tika towen ተብላ በምትጠራ ትንሽ ከተማ ውስጥ በህገወጥ የሰዋች ዝውውር ላይ ተሳታፊ በሆኑ ሰው ሻጭ የእፍኚት ልጆች አማካይነት በተከራዬት ቤት ውስጥ እነዚህን ወጣቶችና በእድሜ አነስተኛ የሆኑ ለጋ ታዳጊዋች በአንድ ክፍል በማጎር ለተወሰነ ቀን ከዚህ ቀደም እንደሚያረጉት እንደልማዳቸው ወጣቶችን አፍነው በማቆየት ወደ ደቡብ አፊሪካ ለመላክ የተያዘው እቅድ ግን አልተሳካም
በአካባቢው ሰዋች ጥቆማና በኬንያ ፓሊሶች ክትትል እነዚህ ምንም የማያውቁ ነገ የተሻለ ኑሮ ትኖራላችሁ በሚል ስብከትና አጉል ተስፋ ተታለው ከፍተኛ ክፍያ በመክፈል ወደ ደቡብ አፊሪካ ለመሄድ የታቀደው እቅድ ሳይሳካ በኬንያ ፓሊስ እጅ ይወድቃሉ ሁኔታው በጥሞና ሲከታተል የነበረው የኬንያ ፓሊስ እነዚህ 34 ኢትዮጵያ በመያዝ እዛው ትንሽ ከተማ ውስጥ በሚገኘው juja police divisonal head quarters በሚባል ፓሊስ ጣቢያ ውስጥ ያስራቸዋል በተያዙ በማግስቱ እዛው ትንሽ ከተማ ፍርድ ቤት በመቀርብ ሰው ሀገር ላይ በህገወጥ መልኩ በመግባታቸውና ማንነታቸውን የሚገልፅ ምንም አይነት ማስረጃ ወረቀት እጃቸው ላይ አለመኖሩን ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን በማጣራት 27 ላይ የአራት ወር እስርና እስራቸውን ሲጨርሱ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱና ይወስናል ቀሪዋቹ ሰባት ወጣቶች እድሚያቸው ለፍርድ ያልደረሰ በመሆኑ በአስቸኮይ ወደ ኢትዮጵያ ይመለሱ የሚል ፍርድ በመፍረድ ፍርድ ቤቱ አማካኝነት ውሳኔው ይተላለፋል
ይሄ ፍርድ ቤት እነዚህ ኢትዮጵያውያን በቀረቡ በአንደኛው ቀን 27ቱ ወደ ከርቸሌ እንዲጎዙ ሲያረግ ሰባቱ ደግሞ እዛው ፓሊስ ጣቢያ ቆይተው ወደ ኢትዮጵያ ዲፖርት ወይም ይመለሱ ዘንድ ወስኖል ። እኔ ግን ወጣቶችን በዛች ጠባብ ክፍል በአካል አግኝቼ ሳዋራቸው በህገ-ወጥ ደላሎች ተታለው ከሀገራቸው ደቡብ ክልል ተነስተው ወደ ደቡብ አፊሪካ ለመሄድ ማሰባቸውንና አሁን ግን ሁሉም ነገር እንደጨለመባቸው ሲያጫውቱኝ እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ አይዞቹህ ከማለት ውጪና በእጄ የያዝኮትን ከወገን በመጠየቅ የእለት ውሃና ምግባቸውን በመግዛት ከዚህ ውጪ ሌላ ማድረግ እንደማልችል በማስረዳት ተሰነባብቼ መውጣቴን እናም በሁለተኛ ቀን አሻራ ሰጥተው ወደ ሀገራቸው ሊገቡ መሆናቸውን ሲነግሩኝ እጅግ ደስታዬ ብዙ ሆኖ ተመለስኩኝ የሚገርመው ግን እኔ ለማጣራት አስቤ እዛው ከተጠቂዋቹ ጋር በአካል ተገኝቼ የጠየኮቸው ጥያቄዋች አለ ወጣቶች ማን ሊረዳችሁ መጥቶ ነበር ብዬ ነበር በመጀመሪያ የወጣቶችም መልስ ማንም መጥቶ ጠይቆን አያውቅም ነው !!! #
የዋህ_ነህ_ወይ_አትበሉኝና ~~~ በዚህ ናይሮቢ ኬንያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤንባሲ ተብየው በዚሁ ናይሮቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ተብሎ EBS ላይ ኬክ ሲቆርሱ የነበሩ ግለሰቦች ወይም ልክ እንደ ዜጋ በናይሮቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሀይማኖት መድሀኔአለም ቤተክርስቲያን እንዲህ ስደተኛ ወገን ዜጎች ሲንገላቱ የሰው ልጅ እንደከብት ሲሸጥ ሌሎችም የሀይማኖት ተቆማት ድምፅ ሳያሰሙ ዝም ማለት ወይም ዝምታው እስከመቼ ነው ወገን እያለቀ: በተረፈ ግን @~~ ይህ ሁሉ ወገን ሲሰቃይ ሲንገላታ ሲጉላላ እንደሸቀጥ ሲሸጥ በቃ ልንል ይገባል ወገን በተቸገረና በተጨነቀ ሰአት ከጎን መቆም ካልቻለ ምኑን ነው ኢትዮጵያውያንን የሚወክለው ጠንከር አርጌ እነዚህ ኢትዮጵያውያንን እንወክላለን የሚሉ አካላትን መጠየቅ የምሻው እውን ይሄን ዜና አልሰሙ ይሆን ? ወይስ በዚህ የሰዋች ንግድ ላይ እጃቸው አለበት የሚለውን ጥያቄ ይመልሱልኝ ዘንድ ነው ? በዚህም የወገን ጉዳይ ላይ አይናቸውን ሳያሹ ዜናውን ሰምተው ድንገት ተርበው ይሆናል በማለት አቅማቸው የፈቀደውን ያደረጉ ትልቅ ምስጋና የሚገባቸው ሁለት ቅን ኢትዮጵያን habtamu tadege እና gelila legesse የተባሉ ድንቅ ኢትዮጵያውያን ለእነዚህ ወገኖች ምስጋና አቀርባለሁ ለአራት ቀን የሚሆን ምግባቸውንና ውሃ ገዝተው እንዲበሉ አድርገዋል ኢትዮጵያዊ ወገንተኝነታቸውን በተግባር አሳይተዋል እናም የኢትዮጵያ አምላክ ውለታችሁን ይመልሳላችሁ ከማለት ውጪ ሌላም የለኝ ። #ግን_እስከመቼ ??? #ኢትዮጵያ_ለዘላለም_በክብር_ትኑር

ጣራው ለሚያፈስ ቤት -የወለል እድሳት፣ – ይገረም አለሙ

By ሳተናውJune 23, 2017 01:56


መላ አከላቷን ዝንጀሮ እሾህ ወግቷት
መቆም መራድ መቀመጥ ተስኖአት
የትኛውን እንንቀልልሽ ብለው ቢጠይቋት፣
ብታስቀድሙልኝ የመቀመጫየን
እኔ እነቅለዋለሁ ቁጭ ብዬ ሌላውን ፣
በማለት መለሰች
ቅድሚያ የሚሰጠውን ነገር ስላወቀች ፡፡
ጣሪያው በሚያፈስ ቤት ውስት እየኖሩ ክረምት በመጣ ቁጥር እየተሰቃዩ በጋ  ሲሆን የወቅት መለዋወጥ የተፈጥሮ ባህርይ መሆኑ ተዘንግቶ ነገር አለሙን በመርሳት ወለሉን ቢያድሱት ግድግዳውን ቀለም ቢያብሱት አይቀሬ ነውና ክረምት ሲመጣ የሚሆነውን አስቡት፤ከንቱ ልፋት አጉል ብክነት፡፡
የቤቱ ወለል እድሳት ቢሻ፣ ግድግዳው ቀለም ቢያምረው፣ ጣራው ደህና እስከሆነ ድረስ መኖር አይከለክልምና ቅድሚያ መቀመጫየን እንዳለችው ዝንጀሮ መቀመጫን አስተካክሎ ሌላ ሌላውን በሂደት ቀን ሲፈቅድ አቅም ሲጎለብት ማደስ ይቻላል፡፡ ጣሪያው የሚያፈስ ቤት ውስጥ እየኖሩ ክረምቱ አልፏል ብሎ ወለል ማደስ ቅድግዳ ቀለም መቀባት ግን አንድም ሞኝነት ሁለትም አጭበርባሪነት ነው፡፡እንዲያም ሲል ከዛሬ ያለፈ አለማሰብ ይሆናል፡፡በአን ጎራ ካለነው እኛ ከምንባለው እነማን ከየትኛው ጎራ እንደሆኑ  እናንተው አስቡት፡፡
ሀገራችን ቤታችን ናት፤ ጣራዋ በብልሽትም በእርጅናም ተበለሻሽቶ በበጋ ለጸሀይ ሀሩር፣ በክረምት ለዝናም ዶፍ ብንዳረግም  ለምደን ተላማምደነው  እንኖራለን፡፡ገዢዎቻንም የእኛ ቻይነት፣ የፈረንጆቹም ጩኸት እንዴትነት ገብቷቸው ወለሉን እያደሱ፣ ግድገዳውን ቀለም እየቀባቡ  ለአላፊ አግዳሚውም ሆነ ለደርሶ ሀጅ ጎብኝው ችግሩ አንዳይታወቅ አንደውም ያማረ የሰመረ መስሎ አንዲታይ በማድረግና መኖሩን ችለውበታል፡፡ ያማረው ቤታችን ሞንዳላው ኑሮአችን እያሉ በሚያሰሙት ፕሮፓጋንዳም እኛን እያደነቆሩም አቀጣጫ እያሳቱም ከፈረንጆቹ ጋር እየተሞዳሞዱ ረብጣው ሳይነጥፍባቸው፣ ዲፕሎማሲያዊው ድጋፍ ሳይቋረጥባቸው፣ሲገድሉና ሲያስሩ የሚሰማው ተቃውሞም ከቃል ወደ ተግባር ሳይሸጋገርባቸው ሀያ ስድስት ዓመት እንደዋዛ ገዙን፡፡ ሁሉንም ነገር አይተው ገምተው ጠብ- መንጅቸውንም ተማምነው ገና አርባ አመት አንገዛችኋለን እያሉ ነው፡፡ ይበሉ! የታገሉት ለምንና ለማን ሆነና፡፡ ጥያቄው እኛ የምንባለው ከተቃውሞው ጎራ ያለነው ብዙ እኛዎች ያለፈውን የሰሩትን እያየን የወደፊት ምኞት ዝግጅታቸውን እየሰማን ምን አልን ምንስ አደረግን ነው ? ብዙዎቻችን ካለንበት ነቅነቅ ያላልነው  ከመማረር ወደ ማምረር ተሸጋግረን  ራሳችንን ከሰቀልንበት ከፍታ አውርደን ከመጯጫህ ወጥተን  አገዛዝ በቃን በማለት  የምንችለውን ጠጠርም ቢሆን ለማስቀመጥ ዝግጁ ነን ወይ? ነው ጥያቄው ይህ ካልሆነ ወያኔ ከምኞት ፍላጎቱም በላ ይገዛናል፡፡ አንደ አያያዛችን ከሆነ ብዙዎቻችን በአፋችን እንጮሀለን እንጂ በወያኔ የተፈጸመው ነገር ሁሉ ውስጣችን ዘልቆ አልተሰማንም ለዚህም ነው ከመማር ወደ ማምረር መሸጋገር ያልቻልነው፡፡ ይህ ባይሆንማ ኖሮ ወቅት እየጠበቀ ወያኔ በሚሰጠን መጫወቻ ከአንልፋችን እየባነንን በምናሰማው ውግዘት ጩኸት  ጣሪያው ለሚያፈስ ቤት የወለል እድሳት የምንጠይቅ ባልሆነ ነበር፡፡ በእኔ እምነት ጣራው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ነው፡ እንደ አብርሀም ሊንከን አባባል የህዝብ፣ በህዝብ፣  ለህዝብ፣  የሆነ መንግሥት ፡፡ ስለሆነም ይህ በሌለበት/በተነፈግንበት/ ሀገራችን  ሌሎች የህግም በሉት የሰብአዊ መብት፣ የቋንቋም በሉት የሀይማኖት ጥያቄዎችን ማንሳት  ታሰርን ተሰደድን ተገደልን እያሉ መጮህ ከሂደቱ ለማትረፍ እንጂ ከግቡ ለመድረስ የማንታገል ያስመስላል፡፡
ዴሞክራሲ ቅንጦት ተደርጎ በሚታይበት አገዛዝ ውስጥ እየኖሩ ስለ ቋንቋ፣ስለ ሀይማኖት፣ስለ ብሄር ብሄረሰብ፤ስለ ህግ በላይነት፣ስለ ሰብአዊ መብት መከበር ስለ ነጻ ምርጫ ወዘተ ማሰብ፣  መጠየቅ፣ መጮህ ጣራው በሚያፈስ ቤት እየኖሩ ወለል ለመቀየር ግድግዳ ለማደስ የመንደፋደፍ ያህል ነው፡፡ እነዚህ ጥያቄዎች ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ሲሆን ምላሽ የሚያገኙ ናቸው፡ ብቻ ሳይሆን ያለ እነዚህ ተግባራዊነት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሊኖር ስለማይችል ወያኔ በሥልጣን ለመቆየት ጠመንጃውን እንደሚተማመን ሁሉ በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ ለሥልጣን የሚበቃ ግለሰብም ይሁን ፓርቲ እነዚህን ነገሮች ማክበርና ማስከበር የህልውናው ጉዳይ ይሆናል፡፡ ስለሆነም ከፈረሱ ጋሪው የሆነውን መያዣ መጨበጫ ያጣውን ነገራችንን በማስወገድ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እውን ማድረግ በሚያስችለው መንገድ አንደየአቅማችን እንራመድ፡፡ለዚህ ደግሞ ቀዳሚው ነገር ራስን መለወጥ ነው ፡፡ እዚህ ላይ አንድ ዘመን ተሸጋሪ አባባል ብጠቅስ ማለት የፈለኩትን ይበልጥ የሚያሳይልኝ መሰለኝና እነሆ!
የአሜሪካፕሬዝዳንት የነበሩት አብርሀም ሊንከን ለኮንግረስ ያስተላለፉት ሁለተኛው መልዕክታቸው ተብሎ በሚጠቀሰው ንግግራቸው «አንድ ትውልድ ያልፍና ሌላ ትወልድ ይተካል፣ ዓለም/መሬት ግን ለዘለአለም ትኖራለች፡፡ ጸጥ ረጭ ያለው ያለፈው ግዜ ፍልሰፍናዎች (ዶግማስ) አውሎ ነፋሳዊ ለሆነው ለዛሬው ችግር ለመፍትሄነት አይመጥኑም፡፡ ጊዜያችን ችግር ያዘለ ስለሆነ በአዲስ ሁኔታ ማሰብና በአዲስ ሁኔታም መንቀሳቀስ አለብን፡፡ ራሳችንን ከሰቀልንበት ከፍታ ማውረድ ይገባል፡፡ ያን ግዜ አገራችንን ለማዳን እንችላለን፡፡ ታሪክን ልናመልጥ አንችልም፣ልንሸሸው አይሆንልንም፣ ክፉም ሰራን ደግ እንዘከራለን፣ (እንታወሳለን) ግለሰባዊ መታወቅ ወይም አለመታወቅ አንዳችንንም ሆነ ሁላችንን አያተርፈንም፣የምናልፍበት እሳታዊ ፈተና (ፍርድ) በክብር ወይንም በውርደት ማለፋችንን ይመሰክራል»
ብዙዎች እኛ ፤ እነርሱ ወያኔዎች ምንም በሉዋቸው ምን ባነገቡት ዓላማ ሊደርሱበት በሚያስቡት ግብ አንድ ናቸው፡፡ በዚህ ጉዳይ አይደለም ሰው ነፋስ አያስገቡም፡፡እንዲህም በመሆናቸው ነው ታግለው ያሸነፉት፣ ሀያ ስድስት ዓመታትም በዙፋኑ ለመዝለቅ የበቁት፡፡ በተቃውሞው ሰፈር ያለነው እኛ ግን ብዙ እኛዎች ነን፡፡ ሰንደቅ ኣላማ ለብሶ ከሚፎክረው፣ ኢትዮጵያ እያለ ከሚዘምረው፣ የብሄር ኩታ ለብሶ ከሚያቀነቅነው ፖለቲከና አይደለሁም እያለ ከሚሸውደው  ወዘተ ብዙ እኛዎች መካከል  የቤታችን ጣራ ተቀይሮ ሁላችንም የጸሀዩ ሀሩር ሳጠብሰን፤ የክረምቱ ዝናም ሳያበሰብሰን መኖር የምችልበት ቤት እንዲኖረን ምን ያህሉ ነን ከምር የምንሻው ተብሎ ቢጠየቅ  ከብዙዎቹ ተግባር በማየት የምናገኘው ምላሽ አሉታዊ ነው የሚሆነው፡፡ ይህ ለወያኔ ግዞት ያመቻቸን መሰረት አልባው ልዩነታችን መሰረት የለሽ በመሆኑ ለገላጋይ ዳኛ ለመካሪ ሽማግሌም የሚመች አይደለም፡፡ ብዙዎች በቤታችን ጣራ መቀየር በየግላቸው ያምናሉ፣ነገር ግን ይህን እምነት የጋራ ለማድረግ ይቸገራሉ፣ለምክንያትነት የማይበቃው ሰበባቸው የሚያሳብቅባቸው ደግሞ ጣራው እኔ በምለውና በምፈልገው መንገድ ካልሆነ በስተቀር ባይለወጥ ይቅር የሚሉ ከራስ በላይ የማያስቡ መሆናቸው ነው፡፡ በግልጽ ቋንቋ ለመናገር እኔ አባዋራ የማልሆንበት ቤት አንኳን ጣራው ግድግዳውም ይደርመስ የሚሉ ነው የሚመስሉት፡፡
አንዳንዶቹ ደግሞ ለስሙ ከተቃውሞው ጎራ ከትመዋል እንጂ አድራጎት ንግግራቸው የተቃውሞ አይደለም፡፡ ጣራው እያፈሰሰም ለጸሀይ እየዳረገም ቢሆን ወለሉ ከታደሰ ግድጋዳው ቀለም ከተቀባ ርካታ የሚሰጣቸው አይነት ናቸው፡፡ ያ ባይሆን  ከሀያ ስድስት አመታት አገዛዝ በኋላ ዛሬ ስለ ህግ በላይነት፣ ስለ ሰብአዊ መብት መከበር፣ ስለ ሀብት እኩል ተጠቃሚነት፣ ስለ ፍትህ ወዘተ ለወያኔ  ማላዘኑ በቆመ ነበር፡፡ እነዚህ ከእባብ እንቁላል እርግብ የሚጠብቁ ሊባሉ የሚበቁ ይመስለኛል፡፡ ሌላው ሁሉ ቢቀርና ቢረሳን  የህዝቡ ጥያቄ ትክክል ነው፣ የሰጡትን ዝም ብሎ የማይቀበል ጠያቂ ትውልድ ፈጥረናል ወዘተ ብለው ተመጻድቀውና ተሳልቀው ለተቃውሞ መውጣቱም ሆነ ያነሳው ጥያቄ ትክክል ነው ያሉትን ህዝብ በገፍና በግፍ አስረው እያስተማርነው ነው ተሀድሶ እየሰጠነው ነው ከሚሉ ሰዎች ምን ሊገኝ ጥያቄ እንደሚቀርብ ጩኸት እንደሚሰማ አይገባኝም፡፡
እያዩያ አለማስተዋሉ፣እየሰሙ አለማዳመጡ፣ እያነበቡ አለመገንዘቡ በእኛ ሰፈር በመብዛቱ እንጂ ወያኔዎች ከጅምሩ በመቃብራችን ላይ ሲሉ በግልጽ ነግረውናል፡፡ጽፈው አስነብበውናል፣ በተለያየ መንገድ በዘፈንም በፊልም አሳይተውናል፡፡እኛ ሰፈር ግን በምኒልክ ዘመን የደነቆረ ምንይልክ ይሙት እንዳለ ይኖራል እንደሚባለው ሆነን በወያኔ ድል ማግስት የተጀመረው ጩኸት፣ልመና ተማጽኖ፣ ስድብ ዘለፋ የመግለጫ ተቃውሞ  ወይ መሻሻል ሳይሳይ ወይ አርጅቶ ገለል ሳይል እስካሁን አለ፡፡
ሎሬት ጸጋየ  ገብረ መድህን የአባቶቻችን ነገር ሳስታውሰው ትዝ የሚለኝ ከሞከርነው ነገር ይልቅ ያልሞከርነው ነው የሚቆጨኝ እንዳለው  እስከ ዛሬ የመጣንበት የፖለቲካ ጨዋታ አላዋጣም፣ የያዝነውም ተለይይቶ ጉዞ  ከምንለው ቦታ የሚያደርስ አልሆነም ስለዚህ ራሳችንን ፈትሸን፣ አመጣጣችንን ገምግምን ድክት ጥንካሬአችንን ለይተን፣ለዘመኑ የሚስማማውን አስተሳሰብ እንያዝ፣ ለትግሉ የሚመጥነው መንገድ እንከተል በማለት የሚታትሩ ብቅ ሲሉ ከወያኔ ሰፈር ባልተናነሰ ጩኸቱ የሚበዛውም ሆነ  ትንሽ ትንሽ መሰናክል ማስቀመጥ የሚጀመረው እኛ ከምንባለው ብዙዎቹ እኛዎች በኩል ነው፡፡
ቤቱ ጣራው ዝናብ ቢያፈስም፣ ጸሀይ ቢያስመታም ወለሉ ካማረ፣ ግድግዳው ቀለም ከተቀባባ ለእኔ ይመቸኛል፤ የጣራው ነገር አያስጨንቀኝም ማለት መብት ነው ምርጫ ነው፡፡ ለዴሞክራሲ ነው የምታገለው የሚል ሁሉ ይህን ምርጫ መቀበል የሰዎቹን መብት ማክበር ይገባዋል፡፡እነርሱ ደግሞ ጣራው መቀየር አለበት ብቻ ሳይሆን ካልተቀየረ በቤቱ ውስጥ መኖር አንችልም በሚለው ወገን እየተከለሉም እየተመሳሰሉም እያደናገሩም መኖሩን አቁመው አቋማቸው ጥቅም የሚያገኙበት ሳይሆን ከልብ የሚያምኑበት ከሆነ   መብታቸውን በይፋ መጠቀም እምነታቸውን በግልጽ ማራመድ ይኖርባቸዋል፡፡መሸፋፈን ለመኝታ ግዜ ብቻ ይሁን፡፡ ማለባበስ ይቁም!
በጣም አስቸጋሪው መፍትሄ አጥቶ የግዞት ዘመናችንን እያራዘመው ያለው በጣራው መቀየር ላይ ልዩነት ሳይኖር መቀየር ያለበት እኔ በምለው መንገድ ብቻ ነው የሚለው አስተሳሰብ ነው፡፡የነገሩ ክፋት የሚብሰው ደግሞ የዚህ አስተሳሰብ አራማጆች በሚሉት መንገድ ለመቀየር ስንዝር የተግባር እንቅስቃሴ የማያደርጉ መሆናቸው ነው፡፡ተግባሩ ቀርቶ እንዴት በምን ሁኔታ በማን ጣራው መለወጥ እንደሚችል ግልጽ አቋም የላቸውም፡፡ አቋማቸውን ገልጸው መንገዳቸውን አሳይተው ሊደርሱበት የሚያልሙትን ግብ ነግረው ደፋ ቀና በሚሉት ላይ ለመዝመት ግን እንቅልፍ የላቸውም ፡፡እንዲህ መሆን የለበትም፣ አንደዚህ ለምን ይደረጋል፣ በዚህ መንገድ ለምን ይኬዳል ከማለት በስተቀር እንዲህ ይሁን በዚህ መንገድ መሄድ ያዋጣል ወዘተ በተግባር ቀርቶ በቃል ደረጃ እንኳን አይናገሩም፡፡
ግልጽ አቋም በጣራው መለወጥ ላይ፣ የቤታችን ጣራ ከተለያየ አቅጣጫ ብዙ ስም የወጣለት ገዢዎቻችንም ሊያደናብሩንና አቅጣጫ ሊያስቱን በከጀሉ ቁጥር አዳዲስ ስም እያወጡ  በአንድ ያልረጉበት ሲሆን የምንሻው ግን ግልጽ ነው፡፡ዴሞክራሲያዊ ጣራ፡፡ ወራጅና ማገሩ ቆርቆሮና ምስማሩ በህዝብ ለህዝብ የህዝብ ሆኖ የሚሰራ ጣራ፡፡ይህን የሚጠላ ወይንም የማይፈልግ በአንደበቱ ባይናገረውም በተግባሩ እንለየዋልን፡፡የመጀመሪያው ወያኔና በዙሪያው ተኮልኩለው ተጠቃሚ የሆኑት ናቸው፡፡ለጥቆ የምናገኛቸው ሀያ ስድስት አመት ሙሉ ተቀዋሚ መባል ያልሰለቻቸው ምን አልባትም የሚያኖራቸው ወያኔ ተሰናብቶ ዴሞክራሲያዊ ሥርኣት ቢሰፍን ወለሉ ይታደስ ግድግዳው ቀለም ይቀባ አይነት የይስሙላ ተቃውሞ እያሰሙ መኖር አይችሉምና የጣራውን ለውጥ አይፈልጉትም፡፡ ሲስልስ ወያኔን ከማውገዝና ከማጥላላት ባለፈ የተጀመረም ሆነ የተሰነቀ ነገር የማይታይባቸው ነገር ግን ይህንኑ መኖሪያቸው ያደረጉ እናት ኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ብሉኮ ብትከናነብ ህዝባችን ተገደለ ታሰረ በዘራችን ብቻ ተጠቃን  እያሉ ነሸጥ ሲያደርጋቸውም በመገንጠል እያስፈራሩ፣ ሰከን ያሉ እለት ደግሞ ስለ አንድነት እየዘመሩ ያሉ፣ የሚኖሩ ወገኖች ያኔ ይህን ማድረግ አይችሉምና በአፋቸው የሚናገሩት/የሚነግዱበት  ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በተግባር እውን ሲሆን ለማየት ይሻሉ ብሎ ማሰብ ይቸግራል፡፡
በድርድርም በሉት በግርግር፤በሰላማዊ ሰለፍም በሉት በጩኸት፣በጽሁፍም ይሁን በንግግር የሚቀርቡ ጣራውን በመለወጥ ላይ የማያተኩሩ ነሮች ሁሉ ጣራው ለሚያፈስ ቤት የወለል እድሳት የመፈልግ ያህል ነውና ሲብስም እቅጣጫ የሚያስት ትግል የሚያዘናጋ ለገዢዎች እፎይታ የሚሰጥ ወዘተ ነውና ይታሰብብት፡፡ በሁሉም መንገድ በየትኛውም መስመር ትግል ጣራውን ለመቀየር፡፤

Thursday, June 22, 2017

ሰራዊቱን ዝም ለማሰኘት የታቀደ የመጀመሪያ ዙር ስራ የተቃዋሚ ደጋፊ የተባሉ ወታደሮችን ለማጥቃት የታቀደ ግምገማ ሊደረግ መሆኑ ታውቋል ቆንጂት ስጦታው



ቆንጂት ስጦታው – ከጦር ሃይሎች የተገኘው መረጃ እንደተመለከተው በመከላከያ ሰራዊቱ ሁሉም እዞች በወታደሮች ላይ ግምገማ ሊደረግ መሆኑ ታውቋል::የግምገማው ዋናው ሂደት በሰራዊቱ ውስጥ የተገኘው የኢሕአዴግ ድምጽ አነስተኛ መሆኑ እና ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ከሚል አንጻር ተጠርጣሪ የተቃዋሚ ደጋፊ የተባሉ ወታደሮችን ለማጥቃት የታቀደ ግምገማ ሲሆን በግምገማው ላይ ሞባይሎች እንደሚፈተሹ እና ተቃዋሚዎችን በተመለከት ውስጥ ለውስጥ ፕሮፓጋንዳ ያራግባሉ እንዲሁም አለማቀፍ ጉዳዮችን በተመለከተ ከሚዲያ መረጃዎችን ይዘው መተው ያወራሉ የሚባሉ ወታደሮች የግምገማው ሰለባ እንደሚሆኑ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ተናግረዋል::የመከላከያ ሰራዊቱ ከሲቭል ደህንነት እና ከኢንሳ በተመደቡ እና የወታደሩን ካኪ ለብሰው በመመሳሰል በሚሰልሉ የሕወሓት አባላት አቅራቢነት ወንጀሎች ተቀነባብረው ግምገማውን እንደሚያጦዙት ይጠበቃል ሲሉ ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል::
የለውጥ ፈላጊ ሃይሎችን ደግፋችሁሃል በሚል ለጥቃት የተዘጋጀው ይህ ግምገማ አለመተማመን እና ጥርጣሬ በሞላው የመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ ልዩነቶችን በማስፋት በአንድ ብሄር የበላይነት የሚተዳደረውን አምባገነን ወታደራዊ አመራርን በማጠናከር ሌሎች ብሄሮች በፍርሃት እና በስጋት እንዲኖሩ ለማሸማቀቅ የሚያደርግ እንዲሁም ሰራዊቱን ለለውጥ ያነሳሳሉ የሚባሉ መኮንኖችን እና ወታደሮችን ሰብስቦ ለማሰር እና ደብዛቸውን ለማጥፋት የታቀደ እንደሆነ ታውቋል:ግምገማው የሚመራው በተለያዩ እና በጄነራልነት ማእረግ ባላቸው የሕወሓት መኮንኖች ሲሆን ሰራዊቱን ዝም ለማሰኘት የታቀደ የመጀመሪያ ዙር ስራ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ 450 የሕወሓት አባላት ተመልምለው ለወታደራዊ ስልጠኛ በሚል በተለያዩ የምስራቅ አውሮፓ አገሮች ለትምሕርት ሊላኩ መሆኑ ሲታወቅ ከአንድ ብሄር ብቻ ለምን/እንዴት ይህ ሆነ የሚል ጥያቄ መነሳቱን እና ምንም አይነት ምላሽ እንዳልተሰጠው ታውቋል::ምንጮቹ አያይዘው እንዳሉት ልሰላም አስከባሪ ሃይል ከፍተኛ አመራር እንዲሆኑ ለስልጠና የታጩት የሕወሃት አባላት ጉዟቸው እንደማይሰረዝ እና ጉዞውን ለተቃወሙት መኮንኖች ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ሲሉ ገልጸዋል:: ቆንጂት ስጦታው

በአማራ ላይ የተሰለፉ አምስተኛ ረድፈኞች! (ቬሮኒካ መላኩ)

ሳተናው June 21, 2017 23:55      


የሰው ልጅ ታሪክ እንደሚያስረዳን አለም በመንታ ባህሪያት የተዋቀረች ትመስላለች። ሰማይ ስንል መሬት አለ። እሳት ስንል ውሃ አለ ፣ ብርሃን ብለን ጨለማ አለ ፣ አርበኛ ብለን ባንዳ አለ እንደዚህ እንደዚህ እያልን ብዙ ነገሮችን መጥቀስ እንችላለን።
እነዚህ ባህሪያት መገለጫ አንዱ ሰው ነው። የሰውም ባህሪ እንደዚሁ ለየቅል ነው። በሰው ውስጥም ክፋትና በጎነት ፣ታማኝነትና ክህዴት ፣ ሁሉም ተቃርኖ አለ። በአንድ ብሄር ፣ ማህበረሰብ ፣ እንድሁም ቤተሰብ ውስጥ የአስተሳሰብ ዝምድና ከሌለ የስጋ ዝምድና ብቻውን ሰዎችን ማወዳጄት ፣ በአንድ አላማ ስር ማሰባሰብ እንደማይችል ከአንድ ማህበረሰብ ብሎም ቤተሰብ የተገኙ ልጆች እርስ በርሳቸው ሲቆራቆሱ እና ሲጨራረሱ የአለም የትግል ታሪክ ያስተምረናል።
ሰሞኑን ከአማራው አብራክ እየወጡ ራሱን አማራውን ከጀርባ በጦር የሚወጉትን ቡድኖች ወዳጄ ዶ/ር GM Melaku “ዋለልኞች” ብሎ ስም አውጥቶላቸዋል። እኔ በበኩሌ ከስፔኖች ተውሼ “አምስተኛ ረድፈኞች ” በማለት ልሰይማቸው።
ዛሬ በወዳጄ በ GM Melaku ስያሜ መሰረት “ዋለልኞች” በእኔ አጠራር ደሞ ስለ አምስተኛ ረድፈኛ አጠር አድርጌ ልፅፍ ነው። ይችን አጠር ያለች ጦማር መፃፍ ያስፈለገኝ ከሁሉም በላይ የአማራ ብሄርተኝነትን ደንቃራ እና ጋሬጣ ሆኖ እየጎዳው ያለው ” አምስተኛ ረድፈኛ ” የሚባለው ቡድን ነው ብዬ ስላመንኩኝ ነው። አማራን የሚጎዳው በይፋ በጉያቸው ሾተል ፣በጭናቸው ክላሽንኮቭ በያዙ ጠላቶቹ ብቻ ሳይሆን ከጉያው በወጡ የወዳጅ ጠላትም ጭምር ነው።
አምስተኛ ረድፈኛ ማለት ፤ አንድ በሚስጥር የተደራጀ ቡድን ወይም ግለሰብ ሲሆን ፣ ለጠላት በመወገን የራሱን ሕዝብ ጥቅም በማንኛውም መልኩ ከመሀል ሆኖ የሚቦረቡር ማለት ነው።
እንደዚህ ዐይነቱ ጠላት ደግሞ ከለየለት የውጭ ጠላት የበለጠ አደገኛ ነው። ለዚህም ነው አማራ ሲተርት “ፈጣሪዬ እኔ ከጠላቶቼ እራሴን ስከላከል አንተ ከወዳጅ ጠላት ጠብቀኝ” ተብሎ የሚፀለየው።

አምስተኛ ረድፍ የሚለው ሀይለ ቃል በመጀመሪያ ለውስጥ ቦርቧሪዎችን ለመግለፅ የተጠቀመው ስፔናዊው የፋሽስት ጀኔራል ሞላ ነው። ከ1936 እስከ 1939 በተካሄደው የስፓኝ የርስ በርስ ጦርነት ጊዜ ማድሪድ ስትከበብ ፋሽስቱ ጀነራል ሞላ በውስጥ አርበኝነት ስለሚያገለግሉት ደጋፊዎቹ ሲናገር “እኛ ማድሪድን በአራት ረድፍ እያጠቃናት ነው። በከተማይቱ መሃል ደሞ 5ኛ ረድፍ አለን” በማለት ከገለፀው የተወሰደ ነው።
በኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክም “አምስተኛ ረድፈኛ” አማራውን ፍዳ ሲያሳየው፣ ወገኖቹን ሲያስጨፈጭፍና ፣ ለጠላት አጋልጦ ሲሰጠው ታሪክ መዝግቦታል።
አረብ ፋቂህ የተባለው የኢማም አህመድ የግል ፀሃፊ በአረብኛ “Futuh al-habasha” በማለት ፅፎት “the conquest of Abyssinia” በሚል ርእስ ወደ እንግሊዚኛ የተመለሰው መፅሃፍ እንደሚከተለው ያለ “የአምስተኛ ረድፈኞች ” አሰቃቂ ድርጊት ተመዝግቦ አንብቤአለሁኝ … …
“ኢማም አህመድ ጠንካራውንና የማይደፈረውን የአምባ ግሸን ምሽግ ለመስበር ብዙ ሞከረ። እዚህ ምሽግ ውስጥ የሰለሞናዊ ስርዎ መንግስት የነጋሲ ልጆች፣ የልጅ ልጆች፣ ዘመዶች እና ብዙ ሀብት ይገኝ ነበር። ኢማሙ ከቱርክ እና ከፓኪስታን በመጡ መድፍ ተኳሾች ቢሞክርም የክርስቲያኖቹ አምባ የማይደፈር ሆነ። ወታደሮቹም አለቁበት። 3 ወር ሙሉ አምባ ግሸንን ለመስበር ሞከረ የማይቻል ሆነ። ወደ አምባው መውጫ ያለው ሁለት በር ብቻ ስለነበር በሩን ይዘው አልበገር አሉ። በመጨረሻ ኢማም አህመድ (ግራኝ) የአምባ ግሸንን ምሽግ ለመያዝ በውጊያ መሞከርን ትቶ አምባው ካሉ የክርስቲያን ተዋጎዎች መካከል አምባውን አሳልፎ የሚሰጠው ከሃድ መፈለግ ጀመረ። በወርቅ እና በገንዘብ የተደለለ ሰውም ተገኘ።በዚህም መሰረት የግራኝን ጦር በስርቆሽ በር በኩል እየመራ ወደ አምባው በድብቅ አስገባቸውና የክርስቲያኑን ጦር ከጀርባ በኩል አስጨፈጨፋቸው። የአምባ ግሸንም ጠንካራ ምሽግ ተሰበረ።” እያለ ይቀጥላል። The conquest of Abyssinia. Page. 345.
ይሄ ከመፅሃፉ የጠቀስኩት ቁራጭ ታሪክ የሰዎችን፣ የከሃድያንን እርቃነ ማንነት እና የሚያደርሱትን ወሰን የለሽ ጉዳት የሚያመለክት ነው። በአገራችን ውስጥ በታሪካችን ዘርዝረን መንዝረን ሳንመለከተው እየቀረን ይሆናል እንጅ የዚህ አይነት የትውልድ አራሙቻዎች ሲከሰቱ ተስተውሏልም እንማርበትም ዘንድ ተመዝግቧል።
አሁን ከአማራ ህዝብና የአማራን ብሄርተኝነት ለመገንባት በምናደርገው ትግል “የአማራ አምስተኛ ረድፈኞች ” ምን ማለት እንደሆነ የተግባባን መሰለኝ። ያልገባው ካለም አምስተኛ ረድፈኛ ” ማለት ከአማራ ህዝብ አብራክ ወጥተው አማራን ለጠላት አሳልፈው የሚሰጡ ፣ ከጀርባ የሚወጉ ( backstabbers) የአማራን ለምድ ለብሰው እንደ ተኩላ የሚተውኑ ማለት ነው።
አስተውላችሁ ከሆነ እነዚህ አጎብጓቢ ረድፈኞች ሲፅፉም ሆነ ንግግር ሲጀምሩ እንድህ በማለት ይጀምራል… “እኔ አማራ ነኝ ነገር ግን በብሄር መደራጀት አላምንም።” ይላሉ። ይች የአነጋገር ዜዬ መለያ ባህሪያቸው ናት። ለእኔ አደገኛው ይሄ ነው። እነዚህ ሰዎች “አማራ ነኝ” ብለው ይጀምሩና “በብሄርም መደራጀት አላምንም ” ብለው ድስኩራቸውን ቀጥለው የኦሮሞውን፣ የሱማሌውን፣ የትግሬውን፣ የወላይታውን፣ የ80 ውን ብሄር መደራጀት ችግር የለውም ብለውን እርፍ ይላሉ የአማራውን መደራጀት ግን በርበሬ እንዳጠኑት ልጅ ሲያስነጥሳቸው ይውላል።
ከ 500 አመታት በፊት ጠላቶቻችን ፈ ት ለፊት ተጋፍጠው ማሸነፍ ስለማይችሉ እየተጠቀሙ ያሉት በዚህ “በአምስተኛ ረድፈኛው” ቡድን በኩል ነው።
የአማራ አምስተኛ ረድፈኞች የሚሰሙኝ ከሆነ ጥቂት ምክር ቢጤ ጣል ላድርግና ፅሁፌን ልዝጋው። ረድፈኞች ከእናንተ ጋር የአንድ ቤተሰብ እና የአንድ ወገን ልጆች ብንሆንም በአስተሳሰብ አንገናኝም። የአንድ ክልል ፍሬ ብንሆንም ጎራችን ለየቅል ነው። የአንድ ወጥ ባህል ልምድና አካባቢ ውልዶች ብንሆንም ግባችን የተለያየ ነው። ባንድ መልክ ያደግን ብንሆንም በተዥጎረጎረ ባህሪይ ጎልምሰናል። ለእኔ የሚጣፍጠኝ ለአንተ ይመርሃል። ለእኔ የሚጥመኝ አንተን ያቅርሃል። ህዝባችን ያለበት አስከፊ ሁኔታ ቆራጥነትን የሚጠይቅ ሌላው ቀርቶ ከአንድ አብራክና ከአንድ መሀፀን የተገኙትን የአንድ አባትና የአንድ እናት ልጆች የሚያታግል ነው። ነፃነት የሚባለውን ክቡር ነገር ለማግኘት ጠላትን ብቻ ሳይሆን የወዳጅ ጠላትንም መፋለም የግድ ይላልና ትግላችን “ከአምስተኛ ረድፈኞች” እና “ዋለልኞች “ጋርም መሆኑ መታወቅ አለበት።

Monday, June 19, 2017

የኤፈርት ዳሪክተር ኣዜብ መስፍን ማጭበርበር ከትግራይ ህዘብ አይሰወርም – ከኣስገደ ገብረስላሴ ወሚካኤል


By ሳተናውJune 20, 2017 00:58



ባለፉት ቀናት ኣዜብ መስፍን ከዓይጋ ፎሮም ዌቭ ሳይት ጋር የኤፈርት ኩባንያዎች ማለት እንድስትሪዎች ፣ባንኮች ፣እንሽራንሾች ፣ የትራንስፓርትና ኮንስትራክሽን ኮፓንያዎች ፣ የንግድ ማእከላት ፣ የላኪና ኣሰመጭ ኩባንያዎች በሚመለከት ሁኔታቸው ለማወቅ ቃለመጠየቅ ሲደረግላት በጥሞና ሰምቸውኣለሁ።
ኣዜብ ለቀረበላት ጥያቄ የሰጠችው መልስ ከዛ በፊት ከነበሩት የኤፈርት ዳሪክቶሮች ስብሃት ነጋ ፣ ስዩም መስፍን ፣ ኣባዲ ዞሞ ልዩነቱ የነዛ የተራቀቀ ማጭበርበር ፣የኣዜብ መስፍን ያልበሰለ ግለጽ ማጭበርበር ነው የሚለያቸው ። በተረፈ የማጭበርበር ስልታቸው የኣንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ነው ።
የነዛ ተንኮልና ማጭበርበር በኤፈርት ሃብት በለጸገ በላ ጠጣ ሃብታም ሆነ እተባለ 25 ኣመት መሉ የተነገደለት የትግራይ ህዝብ በተለይ በቅርብ በኣጠቃላይ ደግሞ የኢትዮጱያ ህዝብ እያወቀውና እየተቸው እየተቃወሞው ኖሮዋል ኣሁንም ተቃውሞው ኣልበረደም ።
ወደ ኣዜብ መስፍን ማጭበርበርና ሽወዳ ልግባ ፣
አዜብ ኤፈርት የማን ነው ተብላ ስትጠዬቅ የሰጠቹ መልስ ፣
** ኤፈርት የማንም እጅ ጣልቃ ሳይገባበት የትግራይ ህዝብ ነው ኣለች ። ይህ ኣባባል 25 ኣመት ሙሉ ኣደንዝዞን ነረዋል ። ኣዜብ መስፍን ህዝብ በየተኛው የባለቤትነት መብት ነው የህዝብ ነው የምትለን ያለች ? እነዚህ ኩባንያዎች ከመጀመሪያ ጀምረው በባለ ቤትነት የተመዘገቡ 32 የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ እና 4 የህወሓት ነባር ኣባላት የነበሩ በሽምግልና ኣእሙሯቸው የተዛቡ የትምህርት ቀለም ያልቆጠሩ ሁለት ከሽሬ ኣንድ ከኣድዋ ኣንድ ከእንደርታ ነበሩ ። ለምሳሌ ለመጥቀስ ወይዘሮ ነጅያ የተባሉ በዛን ወቅት ከ87 ኣመት እድሜ በላይ ነበሩ ።እኒህ እናት ልጆቻቸው በትግሉ ያለፉ ኣይናቸው ጭራሽ የደከሙ መስማት የተሳናቸው ነበሩ ።
እኒ ኣራት ሰዎች ወደዛ የባለቤትነት መብት ሲገቡ ሆን ተብሎ የህዝብ ነው ብሎ ለመጭበርበር ታሳቢ በማድረግ የተሰራ ነበር ።
ለዚሁ መራጋገጫ 32 ማ /ኮቴና ኣራቱ ኣርሶ ኣደሮች 36ቱ ማለት ነው እያንዳንዳቸው 500 ሚሊዮን ብር ሸር ተመዝገበው ሲያበቁ ፣እነዛ 4ቱ ኣርሶ ኣደሮች የተባሉት እኛ ሽማግሌዎች ስለሆን ለህወሓት ማ / ኮሚቴ ኣውርሰናል ብለው እንዲፈሩሙ ተደረገ ። ይህ ማጨበርበር ኣደለም ?
ሌላስ የትግራይ ህዝብ ለባለ ኣደራ ቦርድ በውክልና ሰጥቷል ብላለች ። መቸ ቀን ? በየተኛው ጉባኤ ? የተወከሉ እነማን ናቸው ? ለመሆኑ ከ5 ሚሊዮን የትግራይ ህዝብ ለምስክርነት የሚቀርብ ኣለን ? ሌላ ቀርቶ የህሓት ታማኝ ካድሬ የሚመሰክር ኣለ ? መልሱ የለም ነው ። ኤፈርት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የሸር ባለቤቶች ማ /ኮሚቴ ህወሓት ፣ቦርድ ዳሪክቶሮች ፖሊት ቢሮ ( ስራ ኣስፈጻሚዎች) ናቸው ። እስከኣሁንም የትግራይ ህዝብ ስለኤፈርት ምንም ግንዛቤም ተጠቃሚም ኣይደለም ። ኣሁን ሲመረው በተለይ ሙሁራን ተማሪዎች ወጣቶች ስለ የህወሓት ሸፍጥ በጥልቀት
እየተረዱ ሲሄዱ ጥያቄ ማንሳት ጀምረዋል ።
+++ አይጋ ፈሮም የኤፈርት ኩባንያዎች ሲጀምሩ የካፒታላቸው ምንጭ ከየትነው ሲላት ? በትግል ጊዜ ከሰተሰበሰበውና ከባንክ ብድር ነው ኣለች ። እዚህ ላይ ለጦርነት ማስፈጸምያ ተብሎ የተሰበሰበ ገንዘብ በብር ዶላር ፣ፓውንድ ፣ ደችማርክ ፣ የሱኡዲ ሩያል ፣ ነዳጅ ፣መድሃኒት ፣ የመኪና መለዋወጫ ወዘተ በቡዙ ቢሊዮን ነበረ ። እኔም በወቅቱ ስንቅና ትጥቅ ትራንስፓር ሃላፊ ስለነበርኩ በሚገባ ኣውቃለሁ ።
እኔ የማልቀበለው ከባንክ ተበድረናል ለሚለው በምክንያት ኣድርገው ለዛቁት ዶሏር ለመመዝበር ይመቻቸው ዘንዳ ሽፋን ሊሆናቸው የተሰራ ድራማ ነው እንጅ ለሁሉም ለተቋቋሙ ኩባንያዎች ማቋቋምያ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶሏርና ፓውንድ ነበር ።ብር ቢሆን በወቅቱ ከነበረ የመንግስት ገንዘብ የበለጠ ነበር ። ያከባንኪ ተበድረናል የሚል ድራማ ለወደፊት ዶሏር ለመመዝበር ኣርቀው በማሰብ የተሰራ ድራማ ነበር ። ምክንያቱም የኩባንያዎች ትርፍ የት ገባ ለሚል ጥያቄ ኣፍ መዝጊያ ብለው ኣዛጋጅተውት የቆዩ ነው ። በዛ የስርቆት እስትራተጃቸው መሰረት ደግሞ 25 ኣመት ሙሉ ለቀረበላቸው ጥያቄ ለማጭበርበር ተጠቅመውበታል ።
ሌላ ኣዜብ መስፍን ስትሸውድ ኤፈርት የገባሬሰናይ ስራ ይሰራል በመሆኑም ለኣካል ጉዳቶኞች ፣ ለታጋይ ቤቶሰዎች አግዘናል በዘለቄታም ለ12 000 ለተሰው ታጋዮች ቤተሰብ ኣግዘናል ፣ እናግዛለን በተጨማሪም በማህበራዊ ኣገልግሎት 12 ሁለተኛ ደረጃ ት /ቤቶች ኣሰርተናል ለገናም እና ሰራለን ኣለች ።
ኣዎን እኔም የምመሰክረው በዋጅራት ፣መሶቦ ፣ሳምረ ፣ኣግበ ፣ ኣጽቢ እያንዳቸው ከ17 ሚሊዮን በላይ ብር የፈጁ ወደ 90 ሚሊዮን ብር ጨርሰዋል ። በመቀሌ ሀጸይየውሀንስ ትቤት 70 ሚሊዮን ብር ወጭ ኣድርገው ሰርተዋል ። መቀሌ እና ኣዲስ ኣበባ የሚገኜው የኣካል ጉዳቶኞች ህንጻዎች በመቀሌ 80 ሚሊዮን ብር ፣በአዲስ ኣበባ 100 ሚሊዮን ብር በድምር 370 ሚሊዮን ብር ሰጥተዋል ። ለኣካል ጉዳቶኞች ለተሰው ታጋዮች ቤተሰዎች ኣግዘናል ለምትለው ኣምና ብቻ የትግራይ ህዝብ ስለጠላቸው ወደሁሉ ስራ ኣንሳተፍም ኣንሰበሰብ ብሎ ሲተፋቸው ለመላሳለስ ተብሎ ለ10 000 የ
ሰው የታጋዮች ወላጆች ድጋፍ ማማለጃ ተብሎ 30 ሚሊዮን ብር ለአንድ ሰው ለኣንድ ጊዜ ብቻ የተሰጠ 3000 ብር ሰጠናል ብለው ነበር ከዛበኃላ ኣልቀጠሉበትም። የተሰጠው ግን ለ10 000 ሰዎች ሳይሆን ለ7000 ሰዎች ብቻ ነው የተሰጠ ለዛው ያለውና የለለው(የመነጠ) የመነጠ ወይ ባዶ የሆነ እየተባለ ልዩነት የተፈጸመ ህዝብ ያጣላ ። አንድ ላም አንድ በሬ ወይ ኣንድ ፍየል ያለው አይሰጥም በማለት ተከልክለዋል ።በትግራይ ግን ቤተሰቦቻቸው ኣባቱ እናቱ ሚስቱ ለጆቹ ጨምሮ የታጋዮች የምልሻ የገጠር ካድሬና አደራጅ ፣ አስተዳዳሪዎች የነበሩ የተሰው ቤተሰዎች የደኸዩ ከ1000 000 በላይ ወገኖች ኣሉ ። በጠሩነቱ ባሎቻቸው ፣ ልጆቻቸው ከህወሓት ጋር ተሰልፈው መስዋእቲ የከፈሉ ከሰሜን ጎንደር ከሰሜን ወሎ የላስታን የሰቆጣ ኣገው ፣ ከሰሜን ሽዋ ፣ከኣፋር
ኣይጨምርም ። ኣዜብ መስፍን ስትዋሽ ግን ለ12 000 የታጋዮች ቤተሰዎች ቀጣይ በሆነ በየወሩ እርዳታ እየሰጠን እየጦርናቸው ነን ብላለች ።
*** ኤፈርት ግን በ2008 ዓ ም ከሱር ኮንስትራክሽን ፣መስፍን እንጅነር ፣ትራንስ ኢትየጱያ ፣ከሰሚንቶ ፋብሪካ በኣመታዊ ግምገማቸው በሃወልት ሰማኣታት ያቀረበቹ ሪፖርት የኣራቱ ኩባንያዎች ብቻ 8 . 6 ቢሊዮን ከወጭ ቀሪ ትርፊ በኣንድ ኣመት እንደ ተገኜ ፣ ኣስታውቃ ለሰራቶኞች በቦኖስ በገፍ ሰጥታ ነበር ።
በ2009 ዓ ም ኣሁንም የኣራቱ ኩባንያዎች የኣመቱ ሽያጭ 27 ቢሊየዮን ሆኖ ። የተጣራ ትርፍ 11 . 4 ቢሊዮን ትርፍ እንደተገኜ ከውስጧ ታማኝ ምንጮች ተናግረዋል እንደበፊቱ እንዳያውጁት የኢትዮጱያ ህዝብ በተለይ ደግሞ የትግራይ ህዝብ እንዳያውቀው ስለሰጉ ነው ።ይህ ሁሉ ትርፊ ሌሎች 28 ኩባንያዎችን ኣይጨምርም ። ታድያ ኣዜብ መስፍን 370 ሚሊዮን እርዳታ ሰጠናል ብላ ስታጭበረብር ኣታፍርም 370 ሚሌን ብር እኮ ለኣዜብ መስፍንና ልጆቻ የኣንድ ወር የመዝናኛ ወጭ ኣትሸፍንም ። በኣንድ ወቅት እኮ በውጭ ሚድያዎች እንደሰማነው መለስ ከመሞቱ በፊት በቡዙ ሚሊዮን ዶሏር የሚቆጠር በሁለት ትላልቅ ሻንጣዎች ሞልታ ይዛ ሎንደን ኣውሮፕላን ማረፍያ ተይዛ ነበር በመለስ ድጋፍ ወይ ከውስጥ የመጡ መረጃዎች እንደ ተናገሩት መለስ ከቶኒቢለር ተነጋግሮ ነው የተለቀቀች ወይ የዳነቹ ። ጥሩ ኣዜብ ባለቹ እንቀበላትና የ20 ኣመት ትርፍ የት ገባ የትግራይ ህዝብ እኮ ታጋሽ ሆኖዋል እንጂ ከናንተ በላይ ኣልፎ ሄደዋል ።ኣሁን ግን ትእግስቱ ሟጥጦ ጨርሰዋል ። ወገኖቼ ያትርፍ 28 ኩባንያዎች ኣይጨምርም ስላችሁ ቅርንጫፎችን ኣይጨምር ። ለምሳሌ ወጋገን ባንክ ፣ኣፍሪካ ኢንሽራንስ ፣ ጉና ፣ ሜጋ ህትመት ፣ በሀገር ደረጃ ተሰማርተው የሚሰሩ ናቸው ።
*** የኣዜብ መስፍን የኤፈርት ድርጅቶች የገባሬሰናይ የህዝብ ፣ የኣካል ጉዳተኞች ናቸው ብላ ማጭበርበር ቦሷ ብቻ የተጀመረ ሽወዳ ኣልነበረም ባለፉት 25 አመታት በትግራይ ህዝብ በኣስተማሪዎች ፣በዩንቨርሲቲዎች ፣ነዋሪ ህዝብ ፣ተቃዋሚ ፓርቲዎች በፓርላማ ፣በምርጫ ወድድር ስለኤፈርት የባለቤትነት ጉዳይ የህጋውነት ጉዳይ ጥያቄ ኣንስተው የህሓት ማ/ ኮሚቴ እነ ስብሀት ነጋ ኣባይ ጸሃዬ ፣ኣርከበ እቁባይ ፣ ኣለም ሰገድ ገኣምላክ ጸጋይ በርኸ መለስ ዜናዊ ፣ወዘተ ልክ እንደ ኣዜብ እየዋሹ ነው የነሩ ።
*** እነዚህ ሰዎች ሲዋሹ ለነገ እንኳን ኣይሉም ለመድረካ ማላቀቅያ ብቻ ትሁን ምን ግዳቸው ። በዛን ጊዜ ጥያቄ ሲመልሱ ኤፈርት የኣካል ጉዳቶኞች ነው ይሉ ነበር ።
እኒህ ሰዎች ይቅርና ኤፈርት ሊሰጡዋቸውስ በነሱ ስም የተቋቋመው በመቀሌና አዲስ ኣበባ የተሰራው ሰማይ ጠቀስ ህንጻ በየወሩ በሚሊዮኖች ብር የሚቆጠር ኪራይ የሚያስገባ ፣ ትልቅ የደረቅና ፈሳሽ መጓጓዣ ኩባንያ የበዙ መኪና በስሙ በባለቤትነት የሚነገድበት ፣ የከፍት ርቢ የውሃ መጣርያ ፋብሪካ ወዘተ ኣላቸው እነዚ ኩባንያዎች ኣካል ጉዳተኞች ከመጤፍም ኣይጠቀሙበትም ። በኣሁኑ ጊዜ የትግራይ የጦርነት ኣል ጉዳቶኞች ከ126 000 ውስጥ ትንሽ የጥሮታ ኣበል የምትሰጣቸው 4600 ሰዎች ብቻ ናቸው ። ኣብዛኞቹ በልመና ተሰማርተው የሚኖሩ ናቸው ። እነዚህ ሰዎች ታመው ህክምና ኣያገኙም እነ ኣዜብ መስፍን ግን ጉንፋን ይዙዋቸው በፈለጉት አገር ሚሊዮኖች ዶሏር ይከፈላቸዋል ።
*** ኣሁን ያለው የፓርቲዎች መቋቋምያ ህገመንግስትና ከዛ የመነጨ የፓርቲዎች መቋቋምያ ኣዋጅ ሲተነትን ፣ማንም ፓርቲ የኢህኣደግ ፓርቲም ጭምር 1ኛ በቀጥታ ይሁን በተዘዋዋሪ የንግድና የእንድስትሪ ስራ አይሰራም 2ኛ ማንም ፓርቲ የራሱ ሬድዮጣብያ ተለብዥን ኣይኖረውንም ። ከምልሳን የሚጠቀምበት መጽሄት ጋዜጣ ብቻ ይኖረዋል ይላል ።
ይህ በኣእላፍ የህዝቦች መስዋእት የጸደቀ ህገመንግስት በህወሓት መሪዎች ተንዷል ኣጋሮቹ ወይ ስሪቱ የሆኑ ፓርቲዎቹም ጭምር ንደውታል ።
ታድያ ኣዜብ መስ የኤፈርት ኩባንያዎች
የሀገራችን ህገመንግስት ኣክብረው የሚነግዱ ፣በሃገራችን ካሉ ባለሃብቶች እንደኛ ግብር የሚከፍል እንደ ኤፈርት የለም ብላ ስትናገር ለማያውቃቸው ሃቅ ይመስለዋል ።
ሚድያው ለኣዜብ መስፍን ሲጠይቃት የኤፈርት ኩባንያዎች በሃገሪቱ ያለው ባለሃብት ሊሰራው የሚችል እያለ ኤፈርት ግን በጥቃቅን ንግድ እየተሰማራችሁ ለድህነት ዳርጋችሁቷል ? ብሏታል ።
የኣዜብ መልስ በጠራራ ጸሃይ ስትዋሽ እኛ የተሰማራነው በሃገር ባለሃፍት ሊሰራው በማይችል እየሰራን ለሱ ለመደገፍ ነው የምንሰራ ያለን ኣለች ።
*** ሃቁ ግን እንገራቹሁ የህትመት ስራ ኣንስተኛ ኩባንያ ነው። በኢትዮጱያ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ማተምያ ቤቶች ኣሉ ።በመቀሌ ብቻ ብንወስድ 10 ትላልቅ ማተሚያዎች ከ20 በላይ ትናንሽ ኣሉ ።ግን የመንግስት ስራ በሃገር ደረጃ የሚሰጠው ለሜጋ ህትመትና ኣሳታሚ ድርጅት ነው ። በመቀሌ ያሉ ማተምያቤቶች እየዘጉና እሸጡ ወደሌላ ክልሎች ሄደዋል ።ሌሎችም የሚገዛቸው ኣጥተዋል እንጅ ከስረዋል ። ትናንሾችም እየሞቱ ናቸው ።
*** መሰፍን እንጅነር ብንመለከትስ ፣ ከመስፍን መመስረቱ በፊት መኪና የሚገጣጥም የኤረክሽ ወይ ፋብሪካዎች የመገጣጠም ስራ የሚሰራ መቀሌ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ5000 ስኬር ሜትር ወይ ግማሽ ሄክታር መሬት ወስዶ በቡዙ ሚሊዮን ብር ወጭ በማድረግ እጅግ ዘመናዊ ዎርክ ሾብ ሰርቶ ስራ የጀመረ ፣ለመስፍን ለሌሎች ባለሃብቶች ያስተማረ ማሩ ተፈራ ነበር ያሁሉ ሃብት ወጭ ኣድርጎ ለመስፍን ያስተማረ ከመቀሌ ተባርሯል ሌሎች ትናንሽ የብረታ ብረት ስራ ፣ኤረክሽን የጀመሩም በመስፍን እንጅነር ተገፍተው እንዲወጡ ተደረጉ ። እንዲዋጡም ተደርገዋል ።የተራ የብረት መዝግያ ስራም በመስፍን ተይዞ ነበር ፣ የትግራይ ባለሃብቶች ሲጨንካቸው ማሩ ተፈራ ተከትለው ኣዲስ ኣበባ ደቡብ ሱዳን ሄደዋል ። ከነሱ ከሸሹ ውስጥ እነ ኣብይ ሃይሉ ፣ኣሸናፊ ሃይሉም ይጠቀሳሉ ።
*** ጉናስ ፣ ጉና በሙሉ የንግድ ስራ በሁሉም በኢትዮጱያ ክልል ያሉ ነጋዴዎች ሊሰሩት የሚችሉ ፣የላኪና ኣስመጭ ፣የችርቻሮ የጅምላ ንግድ ስራ በሞኖፓል በመያዝ በተለይ የሰሚንቶ ለከንስትራክሽን የሚያስልጉ ግብኣቶች ሁሉም ኣይነት ብረታብረት ቆርቆሮ ፣ HRS ፣ ሽኮር ጨው ፣ ወ ዘ ተ በሞኖፓል በመያዝ ፣ቡዙ ነጋዴ ኣፈናቅለዋለ በተለይ በጣም የወረደ የስስታም ስራ ከመሰቦ ስሚንቶ ፍብሪካ ማንም ነጋዴና ነዋሪ ህዝብ በቀጥታ ሊወስድ የሚገባው ስሚንቶ ለጉና ይሰጣልና ህዝቡና ኣከፋፋይ ነጋዴና ቸርቻሪ ለጉና ትርፍ ኣስገኝቶ ከጉና ይገዛል ።
*** ትራንስ ኢትዮጱያ የደረቅና የፈሳሽ ጭነት መማላለሻ ኩባንያም እንደሌሎች እህት ኩባንያዎች የሀገራችን ያገር ውስጥና ከውጭ ወደ ኣገር የሚገባ ሁሉም ኣይነት ጭነት የመንግስት ፣ የፓርቲ ኩባንያዎች ፣ የእርዳታ ጭነት ኣብዛኛው ጭነት ያለጨረታ በስምምነት በተጽእኖ ለትራንስ ይሰጠዋል ለዛው የእርዳታ ድርጅቶች የሚከፈለው በዶሏርና በፓውንድ ነው ወይ በከናዳ ዶላርና በደችማርክ ነው ። ሌሎች የግል የነጥረት ፣ የድንሾ እኩሉ ከትራንስ ኢትየጱያ የማጓጓዝ ኣቅም ቢኖራቸው የትራንስ ጌታ ኣዳሪነት ሳብ ኮንትራት ሆነው ኮምሽን እተቆረጠባቸው የሚሰሩ ናቸው ።
በኣጠቃላይ በኢትዮጱያ ያሉ ግለሰዎች በማህበር ተደራጅተው የትራንስ ኢትየጱያ እጥ ፍ
እጥፍ መኪኖች ቢኖሩዋቸውም የትራንስ ጥገኛ ሆነው መስራት የግድ የሏቸዋል ። ትራንስ ኢትየጱያ ሌላ ቀርቶ በክልሎች ያሉ ዞኖች ወረዳዎች ለሚደረግ መጓጓዣ ለትራንስ ኢትዮጱያ ነው የሚሰጠው።ለዚሁ ሀቅ በሀገራችን ያሉ የትራንስፓር ማህባራት ኩባንያዎችይመስክሩ በተለይ ደግሞ በመቀሌ የሚገኜው ሰላም የደረቅና የፈሳሽ ኩባንያ ማህበር ሊመሰክር ይችላል ።ኣባሎቹ መኪና የገዙበት የባንክ እዳ መክፈል ተስናቸው ከስረው እያለቀሱ ይኖሯለ ።
*** ሱር ኮንስትራክሽን ቢሆን ባገራችን ያለው የመሰረተልማት ስራዎች ኣብዛኛው ያለጨረታ በድርድር ይሰጠዋል ።ቡዙ ኣገር በቀል የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ከደረጃ ኣንድ እስከ ደረጃ ስምንት የስራ ፍቃድ ያላቸው ኮንትራክቶሮች እያሉ ። በደረጃ 5 እና 6 ገብቶ በመስራት ኣገር በቀል ኮንትራክተሮች እንዳያድጉ ወይ እንዲሞቱ ኣድርጓል ። ከሱ ጋር እኩል ደረጃ ያላቸው ኩባንያዎች ስራ የሚሰጣቸው ሱር ኮንስትራክሽ በቃኝ ካለ በኃላ ነው ስራ የሚሰጣቸው ።
*** የቀሩት 28 ግዙፍ ኩባንያዎችም በሙሉ በሌሎች ኣገር በቀል ኩባንያዎች ሊሰሩ እየቻሉ ስለህዝብ ተጠቃሚነት ደንታ የሌለው የህወሓት ኣማራር ግን አዜብ መስፍን እንዳለቹ ለባለሀብቶች የሚያሰለጥንና የሚደግፍ ሳይሆን የህወሓት ተላላኪ ያልሆኑ ባለሃብቶች ሆን ብሎ እንዲነቀሉ ነው እየተንቀሳቀሰ የቆየው ኣሁንም እየተገበረው ያለው ። የመለስ ረኣይ እኮ በሀገራችን ያሉ የንግድ እና የእንድስትሪ የእንጅነሪንግ ኩባንያዎች ከ10 ኣመት በኃላ 100% በኢህኣደግ ኣባል ፓርቲዎችና በመከላከያ ምኒስቴር ፣ ስር እንደሚሆን በግልጽ ኣስሙሮበት ኣልፈዋል ።ታድያ ኣዜብ መስፍን የምታዳናግረው እንዴት ብሎ ተቀባይነት ያገኛል ። እነዚህ ፍጡራን በበረሃ ኣለም የደረሰበት ስልጣኔ እንዳናውቅ ኣፍነውን የኖሩ ኣልበቃም ብሉዋቸው አሁንም ለዚሁ ኣዲስ ትውልድ አጭበርበረው ሊያልፉ ነው የሚፈልጉ ? ፍጹም ኣይሆንም ። ኣይቻልንም ።
*** ጠያቂው ለኣዜብ መስፍን ኤፈርት ግልጽነተ ይጎድለዋል ፣የኤፈርት ሃብት ኦዲት ኣይደረገም ብሎ ሲጠይቃት ?
ኣዜብ ኣይኑ ያፈጠጠ ውሼት ስትዋሽ ፣ሁሉም ኩባንያዎች የውስጥና የውጭ ሂሳብ የሚደርጉ ኣሉ ።የመንግስት ፋይናንስም ኦዲት ያደርጋሉ ብላ ዋሸች ።
ዋዋዋ ለኣዜብ እና ለህወሓት ኣማራር ህዝብ እንዲያውቃቸው የማውቀው እመሰክርላችሁ ኣለሁ ።
ኤፈርት ሲመሰረት ስልጣኑ በህወሓት እጅ በመሆኑ ኣብዛኞቹ ኩባንያዎች መዋቅራቸው ለስርቆትና ለማጭበርበር በሚመች ስለተዋቀሩ
ገቢና ወጭውም ለኦዲት በማይመች መልኩ ነው የተዋቀረው ።
ከ8 ኣመት በፊት በኢፈርት ደረጃ ተጠሪነቱ ለነስብሃት ነጋ የሆነ በኦዲተርነት ከፍተኛ ሙያ ያላቸው ምርጥ እዲተሮች ቀጥሮ የሁሉም የኤፈርት ኩባንያዎች የገቢና ወጭ ሰነዶች ወደ ኤፈርት እየተሰበሰበ ኦዲት ይደረግ ተብሎ ነበር ። ሙሁራኑ የኤፈርት ኣሰራር እጅጉን የተዝረከረከ ስለነበር ፣ ኦዲቶሮች ቡዙ ሃብት ገንዘብ እንደተጠፋፋ እና ወደ ህግ የሚያቀርብ ትልቅ ጉድለት እንዳለው ሪፓርት በማቅረባቸው ፣ እነዛ ቦርድ ዳሪክቶሮች ለኦዲተሮቹ ተጠፋፋ የምትሉት ሃብት ሰርዙት ብለዋቸው ፣ ኦዲቶሮችም ለሙያቸው የሚጻረር ኣሰራር በመሆኑ ኣመታት የጨረሰ የእዲት ስራ መሰረዝ ሂሊናቸው ስላልፈቀደላቸው ከሰራቸው በነስብሃት ነጋ ተገፍተው ተባረሩ ።
ስለዚህ ኣዜብ መስፍን እንደዚህ ኣይነት ኣሰራር የሚከተል ኤፈርት
በጥራት ኦዲት ይደረጋል ብላ ስትናገር ማን ይቀበላታል ?? ።
*** ኣዜብ በቢሊዮን የሚገመት የኢፈርት ብር የት ገባ በማን ቁጥጥርስ ይተዳደራል ሲላት ፣ ለመዋሼት ድንብርጭ የማይላት ኣዜብ ኤፈርት እስከኣሁን የተገኜ ገቢ ለባንክ እዳ ከፈልነው ኣለች ።
የተከበራቹ ኣንባብያን ኣዜብ ቀደም ሲል የኤፈርት ኩባንያዎች የተመሰረትበት ለጦርነት ማስፈጸምያ ተብሎ የተሰበሰበ ገንዘብ ጦርኖቱ ከተቃጨ በኃላ የቀረው በጦርነት ለተጎሳቆለውን የትግራይ ህዝብ ማቋቋማ የሚያክል ቡዙ ገንዝብ ነበረን ብላለች።
እኔም ጦርኖቱ ካለቀ በኃላ በወቅቱ እጅግ ቡዙ ቢሊዮን ብርና ዶላር ፓውንድ ፣ ወርቅ ነበር ። እንዲሁም ዋጋው በቢልዩን ብር የሚቆጠር የተሸጠ መድሃኒት ፣ የምግብ ዘይት ፣ ሽኮር ፣ ነዳጅ የሞተር ፣ዘይት ፣ የተሽከርካሪዎች መቀያየሪ እቃ ፣ ተሸከርካሪዎች ፣ ሌሎች ቁሳቁስ ተሽጠው ቡዙ ቢሌን ብር ነበር ፣ በሱኡዲ ኣረብያ ፣በኢጣልያን ፣ በእንግሊዝ የንግድ ኩባንያዎች ነበሩ ። እነሱም ቡዙ ገንዘብ ነበሩ ይህ ሃቅ እኔ የስንቅና ትጥቅ የትራንስፖርት ስልጣን ስለነበረችን የነበረን የገንዘብ መጠን በሚገባ ኣውቃለሁ ። በወቅቱ የኤፈርት የባለቤትነት ጉዳይ በመቃወም
እስከ በነፍጥ መማዘዝ ደርሸ ነበር ። በመሆኑ ኣዜብ የምትለው ያለች ሁሉ ለትግራይ ህዝብ ማታለል ነው ።
ኣዜብ መስፍን ብድር ነበረን ስትለን ግን የህወሓት ኣማራር ለረጅም ጊዜ የሚሰራ ያስቀመጡት የሸፍጥ እስትራተጂ ለመሸፈን ብላ እያታለለችን ያለች መሆኗ ነው ።
የኣዜብ ስለኤፈርት የባለ ቤትነት ጉዳይ ሌሎች የሸፍጥ ዘዴዎች የተናገረቹ መልስና ኣስተያየት እየቆራረጥኩ እቀጥልበት ኣለሁ ለዛሬ እዚሁ ላብቃ
ከኣስገደ ገብረስላሴ ወሚካኤል ፣
በ13 / 10 2009 ዓ ም

Friday, June 16, 2017

የፕ/ር አስራት ወልደየስ የመቃብር ቦታ ወደ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሊዘዋወር ነው



              

የቀኃስ ቀዳማዊ ገጽ እንደዘገበው የባለወልድ ቤተክርስቲያን እድሳትን ተከትሎ በቤተክርስትያኑ ፊት ለፊት ያሉ መቃብሮች በሙሉ የፈረሱ ሲሆን ዛሬ የ ፕ/ር አስራት ሀውልትም በመነሳት ለይ ይገኛል።
የ ፕ/ር አስራት መቃብር ወደ ቅድስት ሥላሴ በክብር ታጅቦ እንዲዘዋወር እያስተባበሩ ያሉ 9 ሰዎች መሀከል
1, ዶ/ር ያዕቆብ ሀይለማርያም
2, ኢ/ር ግዛቸው ሽፋራሁ
3, አቶ የሺዋስ አሰፋ( ከ ሰማያዊ ፓርቲ)
4, አቶ ሙሉጌታ አበበ ( ከ መኢአድ ፓርቲ)
5, ኢ/ር ጌታነህ ባልቻ ( ከ ሰማያዊ ፓርቲ)
6, አቶ ሸዋንግዛው (ከ መአህድ ፓርቲ)
7, አቶ አክሊሉ (ከ መአህድ ፓርቲ)
ይገኙበታል።

ምንጭ: የቀኅሥ ቀዳማዊ ገጽ